Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • November 2018
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

የዛሬዋ ዓለማችን ይህን ትመስላለች | የፈረንሳዩ ማክሮን ሲቀባጥሩ፣ ሽህ መሀመድ ሲያንኮራፉ፣ ፕሬዚደንት ትራምፕ ሲገላምጧቸው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 15, 2018

በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ህዝብ በአሰቃቂ ሁኔታ ያለቀበት አንደኛው የዓለም ጦርነት ካበቃ ባለፈው እሁድ 100 ዓመት አስቆጠረ። እለቱ ከትናንት በስቲያ ፓሪስ ፈረንሳይ ውስጥ የዓለም መሪዎች በተገኙበት ታስቧል።

በዚሁ የመታሰቢያ ስነስርዓት ላይ የፈረንሳዩ ፕሬዚደንት ንግግር ሲያሰሙ፤ የአረብ ሞሮኮ ንጉስ ሲያንቀላፉ የአሜሪካው ፕሬዚደንት ትራምፕ ክፉኛ ሲገላምጧቸው ይታያሉ።

ለ አንደኛው እና ለሁለተኛው የአለም ጦርነቶች መንሥኤዋ ኢትዮጵያ ናት፦

የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት በአውሮፓ አገሮች መኻል ከ ፲፱፻፮ 1906 /ም እስከ ፲፱፻፲፩ 1911/ም መግቢያ፣ ለአራት ዓመታት የተካሄደ ጦርነት ነው። ይኼ ግጭት የዘመኑ ኃያላን አገራት በሁለት ተቃራኒ ወገን ተሰልፈው ያካሄዱት ግብግብ ሲሆን እስከ ሰባ ሚሊዮን ታጣቂዎች የተካፈሉበትና እስከ አስራ አምስት ሚሊዮን አውሮፓውያን ሕይወታቸውን ያጡበት ትልቅ ጦርነት ነው።

በ ፲፰፻፹ 1880 ዎቹ እኤአ የአውሮፓ መንግሥቶች በበርሊን ጉባኤ ተስማምተው አፍሪካን በቅኝ ገዢነት መከፋፈል ጀመሩ። በኢትዮጵያ እና ጣልያን መካከል የነበሩ የዚያ ዘመን ውዝግቦች ወደ አድዋ ጦርነት በ ፲፰፻፹፰ 1888 ዓም አመሩ። በጦርነቱ የጣልያን ትልቅ ዘመናዊ ጦር በኢትዮጵያ ጦር ትልቅ ሽንፈት የደረሰበት መሆኑ ዓለምን አስደነቀ።

አንደኛው የኢትዮጵያና ጣሊያን ጦርነት በኢጣሊያ እና ኢትዮጵያ መካከል፡ እ..አ ከ1895 እስከ 1896 ድረስ የተካሄድ ጦርነት ነው። የኢትዮጵያ በአድዋ ላይ ድል መቀናጀት አውሮፓን ከፍተኛ ቀውጥ ውስጥ ጣላት።

በቅድመ ፪ኛው የዓለም ጦርነት ወቅትም አገራችን ኢትዮጵያ በ፲፱፻፳፰ ዓ/ም በፋሽስት ኢጣልያ በግፍ መወረር የሁለተኛው የዓለም ጦርነት መነሻ ምክንያት ነበር።

______

Leave a comment