Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • October 2018
    M T W T F S S
    1234567
    891011121314
    15161718192021
    22232425262728
    293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

የጣዖቱ ዋቄዮ ዛፍ ሲመለክበት በነበረበት ቦታ ላይ ተዓምረኛ የ ቅድስት አርሴማ ጸበል ፈለቀ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 10, 2018

በጎጃም ይኖሩ የነበሩ ሁለት ወጣቶች በራዕይ ተመርተው ወደ አዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ በመምጣት ይህችን ተዓምረኛ ጸበል ለማግኘት በቅተዋል። ጸበሏ በፈለቀችበት ቦታ ላይ፡ ከ20 ዓመታት በፊት፡ ጣዖታዊውን አምላክ ዋቄዮን የሚያመልኩት ወገኖች የዋንዛ ዛፉን ቅቤ ይቀቡበት ነበር።

አንድ ሌላ የገረመኝ ነገር፡ ቪዲዮው ላይ እንደሚሰማው፡ አንድ አባት እኔን በቅድስት አርሴማ ጸበል በሚያጠምቁበት ወቅት አንዲት እርግብ በርራ በመምጣት እራሳቸው ላይ ልታርፍባቸው መብቃቷ ነው። በዕለቱ እንዴት ከሩቅ ሠፈር ወደዚህ ቦታ ተመርቼ ለመሄድ እንደበቃሁ አላውቅም፤ ታክሲው ዝምብሎ አወረደኝ፤ ያውም እዚያ የደረስኩት የመጠመቂያው ሰዓት ካለፈ በኋላ ነበር። ተዓምር ነው!

በአዲስ አበባ ለቡ አካባቢ በምትገኘው በዚህች ጸበል ብዙ ሱባኤ የሚገቡ እህቶችና ወንድሞችን ለማየት በቅቼ ነበር።

እንኳን አደረሰን!

______

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: