የ ሰይጣን ባፌሜት ሦስተኛው ሃውልት አሥርቱ ትዕዛዛት ሐውልት ጎን በክሊንተን ከተማ ይፋ ተደረገ
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on August 18, 2018
ዋውው! በደብረ ታቦር በዓል ዋዜማ!!!
ዛሬ፡ እ.አ.አ 08/08/18 ነው!
ከትናንትና በስቲያ፡ እ.አ.አ ኦገስት 16/ 2018 ዓ.ም የሰይጣን ቤተ እርኩስ ውስጥ የፍየል እራስን የሚያሳየው የባፎሜት ሃውልትን ይፋ አድርጓል። ይህ የሰይጣን ሃውልት 2 ሜትር ቁመት ሲኖረው በ አርካንሳስ ግዛት ዋና ከተማ፡ “ሊትል ሮክ ወይም ትንሽ ድንጋይ” (የፕሬዚደንት ክሊንተን አገር)ዋና የማዘጋጃ ቤት አዳራሽ ግቢ ውስጥ ከ ከሚገኘው አሥርቱ ትዕዛዛት ሐውልት ጎን እንዲተከል ተደርጓል።
በደብረ ታቦር በዓል ዋዜማ!
ከዚህ በፊት እ.አ.አ በ2012 ዓ.ም እንዲሁ በኦክላሆማ እና እ.አ.አ በ2015 ዓ.ም ደግሞ በዲትሮይት፡ ሚቸገን እንዲሁ ይህን የሰይጣን ሃውልት፡ ማዘጋጃ ቤቶቻቸው ውስጥ ከአሥርቱ ትዕዛዛት ሐውልት ጎን ተክለውት ነበር።
ይህ ሰነፍና ጨምላቃ ዓለም “አትግደል! አታመንዝር! አትስረቅ! ወዘተ ብሎ በሚያስተምረን ተወዳዳሪ በሌሌው የአሥርቱ ትዕዛዛት ስርዓት ስር መኖር አይፈልግም። ስለዚህም ነው በአይሁድ–ክርስቲያን ዓለሙ ላይ እርኩስ ጣዖት አምላኪዎች ሰዶማውያንን፣ ዮጋ ሂንዱዎችን፣ ቡዳዎች እና እስላሞችን በማሰባሰብ ላይ የሚገኘው።
ፍየል እራሱ ባፎሜት ግንባር ላይ ያለው የሚታየው ኮከብ ሉሲፈራውያኑ መሪዎቻችንን ሰንደቅ ዓላማችን ላይ እንድነለጥፍ ያስገደዷቸው ባለ አምስት ማዕዘን ኮከብ መሆኑ ነው።
ዶ/ር አብይ አህመድ በሚቀጥሉት ስድስት ወራት ይህን ኮከብ እንዲነሳ ካላደረገ እርሱም የባፎሜት ልጅ ነው ማለት ነው።
Leave a comment