Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • August 2018
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    2728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for August 16th, 2018

በጣም አሳዛኟ እህታችን በሳውዲ አረቢያ | በቡና፣ ጥንባሆ እና ሺሻ ያጠምዳሉ፤ ከዚያ ወደ ሳውዲ ይጠሩና ነፍስ ይነጥቃሉ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on August 16, 2018

[መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፻፵፩፥፬]

ልቤን ወደ ክፉ ነገር አትመልሰው፥ ዓመፃን ከሚያደርጉ ሰዎች ጋር ለኃጢአት ምክንያት እንዳልሰጥ፤ ከምርጦቻቸውም ጋር አልተባበር

[ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ ፴፪፥፮]

ሰነፍ ግን ስንፍናን ይናገራል፥ ልቡም ዝንጉነትን ይፈጽም ዘንድ በእግዚአብሔርም ላይ ስሕተትን ይናገር ዘንድ የተራበችውንም ሰውነት ባዶ ያደርግ ዘንድ ከተጠማም ሰው መጠጥን ይቈርጥ ዘንድ በደልን ይሠራል

[፩ኛ የዮሐንስ መልእክት ምዕራፍ ፭፥፲፱]

ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን ዓለምም በሞላው በክፉው እንደ ተያዘ እናውቃለን

______

Posted in Ethiopia, Faith, Life | Tagged: , , , , , | Leave a Comment »

የ አባይ ቁጣ ማክሰኞ ሱዳናዊ ሽብርተኛን ወደ እንግሊዝ ላከ፣ ረቡዕ ፳፬ ሱዳናውያን በሞት ቀጠፈ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on August 16, 2018

ከሁለት ቀናት በፊት በእንግሊዟ ለንደን፡ ብሪታኒያ ምክር ቤት አጠገብ የእግር መንገደኞችንና ብስክሌት አሽከርካሪዎችን ለመግደል አቅዶ የነበረው ሱዳናዊው ሙስሊም በ መኪና አደናቸው።

ይህ ሱዳናዊ ከ ፭ ዓመት በፊት ወደ ብሪታኒያ መጥቶ የብሪታንያን ዜግነት አግኝቷል። የ ፳፱ ዓመት እድሜ ያለው ሳሊህ ካተር ከዚህ ቀደም በዚሁ በዊስትሚንስትር የለንደን ከተማ አካባቢ (ፓርላማው እዚህ ይገኛል) ሽብር ፈጽመው ከነበሩት የበርሚንግሃም ሙስሊሞች ጋር ግኑኝነት እንደነበረው አሁን ተገልጿል።

አይገርምም? እንግሊዞች ለሽብር ፈጣሪዎቹ በ፭ ዓመት ብቻ የብሪታኒያ ዜግነት ይሰጧቸዋል። ፲ ዓመት ቆይተው ዜግነቱን ያላገኙ ኢትዮጵያውያንን አውቃለሁ።

በትናንትናው ዕለት ደግሞ፡ በሱዳን አገር አንድ ፵ ተማሪዎችን የያዘች ጀልባ አባይ ወንዝ ላይ ሰጥማ ፳፬ ሕፃናት ሞቱ፤ ነፍሳቸውን ይማርላቸውና።

ለ ሺህ ዓመታት ውሃውን በነፃ በሚጠጡት ምስጋና ቢሶቹ ላይ እግዚአብሔር ተቆጥቷል፣ በ አባይ ቁጣውን ይገልጻል፦

ይገርማል፤ እንግሊዝ መጀመሪያ ላይ የአባይን ውሃ ለግብጽና ሱዳን ሰጠች፤ ኢትዮጵያ ግን ተጠማች፣ አሁን ግን አምላካችን በቃችሁ አላቸው፤ ኢትዮጵያን የሕዳሴውን ግድብ እንድትሠራ አዘዛት፣ ተንኮለኞቹ ጣሊያኖች “እንርዳ” ብለው ከች አሉ፥ ግብጾች ከከሃዲዎች ጋር ተባብረው ግንበኛ ስመኘውን ገደሉአቤት ድፍረት!

ሱዳን፣ ግብጽ፣ እንግሊዝ፣ ጣሊያን፤ ተውን! አትተናኮሉን፤ ኢትዮጵያን አትንኩ!

አባይ የእግዚአብሔር ወንዝ ነው!

______

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: