Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • August 2018
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    2728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

ተዓምር በሜክሲኮ | እግዚአብሔርን እየለመኑ በሕይወት የተረፉትን መንገደኞች አንድ ክርስቶስን የተቀበለ የቀድሞ ሙስሊም በቪዲዮ ቀርጿቸው ነበር

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on August 2, 2018

ባለፈው ማክሰኞ በነበረው የሜክሲኮ የአውሮፕላን አደጋ መንገደኞች እየሱስ ክርስቶስ በሩን ክፈትልን እያሉ ሲማፀኑ የሚያሳይ አስደናቂ ቪዲዮ ነው።

አውሮፕላኑ ከዱጋንጎ አለምአቀፋዊ አውሮፕላን ማረፊያ በ 3 45 ፒኤም ኃይለኛ አውሎ ነፋስ በነበረበት የአየር ጠባይ ላይ አሽኮብክቦ ለመብረር ሙከራ አድርጓል ይህ ወደ ሜክሲኮ ከተማ ለመብረር አቅዶ የነበረው አውሮፕላ እንደተነሳ ከፍታውን ለመያዝ ሲሞክር፡ እንደገና በመውረድ ማሽኮብኮቢያውን መንገድ ስቶ በመወርወር460 ሜትር ርቀት በሚገኘው ሜዳው ላይ ተከሰክሷል።

የተዓምር ነገር ሆኖ በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩት በአጠቃላዩ 103 ሰዎች፡ ቀሳውስትን ጨምሮ፤ በሕይወት ተርፈዋል። አውሮፕላኑ በድህረፍርስራሽ እሳት ቃጠሎ ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል

ሁለተኛው ክፍል ላይ እንደሚታየው ተዓምሩን በከፊልም ቢሆን በቪዲዮ የቀረጸው አብሮ ይጓዝ የነበረውና፡ እስልምናን በመተው ክርስቶስን የተቀበለው ኢራናዊ ነው።

ሁለት ደቂቃ በሚወስደው ቪዲዮው ላይ፡ አውሮፕላኑ ከመነሳቱ በፊት እና ከአደጋውም በኋላ ከበስተጀርባ ሴቶች፣ ወንዶች እና ሕፃናት ሲጯጯሁ ይሰማል፤ የ እግዚአብሔርን ስም ጮክ ብለው ሲጠሩ እና ኢየሱስ ክርስቶስ ባክህ በሩን ክፈተውበማለት ሲማፀኑ ይሰማሉ።

የቪዲዮው አንሺ ኢራናዊ በትዊተር ገጹ ላይ የሚከተለውን ተናግሯል፦

በእግዚአብሔር ጸጋ ደህና ነኝ፡ እርሱ ይመስገን በህይወት አለን፣ ይህ ሌላ ነገር አይደለም ትልቅ የእግዚአብሔር ተዓምር ነው፣ ሕይወት ስላለሁ ለኢየሱስ ክርስቶስ ብድር አለበኝ፣ ዲያቢሎስ ሕይወቴን ሊወስድ እችላለሁ ብሎ አስቦ ነበር፡ ነገር ግን አሁን እንዲያውም ለ ኢየሱስ ክርስቶስ እራሴን በይበልጥ እንደሰጥ ረድቶኛል

______

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: