Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • July 2018
    M T W T F S S
     1
    2345678
    9101112131415
    16171819202122
    23242526272829
    3031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for July 19th, 2018

ውቡ የድልድይ መናፈሻ | “እውነት ይህ ኢትዮጵያ ነውን?” አሉኝ ፈረንጆቹ…

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on July 19, 2018

ይህን ቪዲዮ ሳሳያቸው።

ከቦሌ ድልድይ እስከ ካዛንቺስ፡ ፀደይ ፪ሺ፲ ዓ.

አንዳንዶቹ ወደ ኢትዮጵያ ሄደው የሚያውቁ ናቸው፡ ግን ደርሰው ሲመለሱ የሚያሳዩአቸው ቪድዮችና ፎቶዎች “በጥቁር መነጽር” የሚያዩአቸውን ወይም ለማየት የሚፈልጓቸውን ነገሮች ብቻ ነው (ኔጋቲቩን፣ መጥፎውን ወዘተ)፤ እጽዋቱን፣ አታክልቶችን፣ አበባዎችንና ለምለሙን ነገር በፍጹም ማየትና ማሳየት አይሹም። ለምን? ምክኒያቱም ኢትዮጵያና አፍሪቃን የሚያዩበት መነጸር በጣም የተለየ ነውና፤ ምክኒያቱም አንጎላቸው በሳሙና ሙለጭ ተደርጎ ታጥቧልና። “የማዝነው ለናንተ ነው” እላቸዋለሁ፤ አይተው እንኳን ማመና መለወጥ ያቅታቸዋልና።

ያ ካናዳዊ የመንገድ ሰባኪ ጓደኛችን እዚሁ ድልድይ ሥር ሆኖ ሲሰብክ ነበር፤ ግን ምን መርጦ እንደቀረጸ፣ ምን ዓይነት ብርሃንና ቀለም እንደተጠቀመ በምስክርነት ማየት እንችላለን።

በዚህ አጋጣሚ፡ እዚህ ድልድይ ስር እነዚህን ውብ አበቦች ለሚንከባከቡት እናቶች አድናቆቴን እገልጻለሁ። እናታዊ ትህትናቸው በጣም ደስ ይላል።

እኛ ዲያስፐራውያን እነዚህን እናቶች፤ በተለይ፤ ቆሻሻ የሚሰብሱብትን እና እንጨትና ጭራሮ ተሸከመው የእንጦጦን ተራራ ለሰዓታት የሚወርዱትንና የሚወጡትን እናቶች ባገኘነው አጋጣሚ ሁላ ልንረዳቸው ይገባናል።

______

Posted in Ethiopia, Music | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ፍቅር? አንድነት? | ፕሬዚደንት ኢሳያስን ለመቀበል የወጡ አንዳንድ ፈረሰኞች ለምን “የኦሮሚያን” ባንዲራ ያዙ?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on July 19, 2018

ይህ ቅዱስ ሚካኤል ዛሬ የመራኝ ክሰተት ነው።

ሁለተኛው ክፍል ላይ “ኦሮሞ ነኝ፤ ኢትዮጵያዊ አይደለሁም” የምትለዋ ከሃዲ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ታቃጥላለች። ለንስሐ ያብቃት!

ለነገሩ ከዚያኛውም ባንዲራ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ፤ የሉሲፈር ኮከብ እስካልተነሳ ድረስ፡ የአንድነትና ፍቅር ጉዳይ ህልም ሆኖ ነው የሚቀረው። ዶ/ር አብይ በሚቀጥሉት ቀናት የሚፈተኑት በሦስት ቁልፍ የሆኑ ነገሮች ነው፤ የሚከተሉትን እርምጃዎች ከወሰዱ፡ ምንም እንኳን በሉሲፈራውያኑ ዘንድ ጥቃት ሊደርስባቸው ቢችልም፤ በኢትዮጵያውያንና በእግዚአብሔር አምላክ ዘንድ ግን ትልቅ ቦታ ሊያገኙ ይችላሉ። ይህም፦

1. በአንግሎአሜሪካውያን ሉሲፈራውያኖች አስገዳጅነት የተገበረውን የብሔር ፖለቲካና ፌደራሊዝም ካፈረሱ

2. በአንግሎአሜሪካውያን ሉሲፈራውያኖች አስገዳጅነት ክቡሩ ባንዲራችን ላይ ያረፈውን ኮከብ ካስነሱ

3. አገራችን ከሉሲፈራውያን አረቦችና ቱርኮች ጋር የምታደርገውን ጥብቅ ግኑኝነት ቀስበቀስ ካላሉት

______

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | 1 Comment »

 
%d bloggers like this: