Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2018
    M T W T F S S
     123
    45678910
    11121314151617
    18192021222324
    252627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for June 29th, 2018

ሳውዲዋ ጋዜጠኛ የእስልምናን አለባበስ ሕገ ደንብ በመጣሷ ለመሰደድ ስትገደደ፤ ኢራናውያን ደግሞ፡ “ሞት ለፍልስጤም እና ለአያቶላ” እያሉ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 29, 2018

የሳውዲ አረቢያ ቴሌቪዥን አስተናጋጇ ሸሪን አልራፊዬ ቪዲዮው ላይ እንደምትታየው ጸጉሯን ሙሉ በሙሉ ባለመሸፈኗ እስራትነና የ100 ጂራፍ ግርፋትን ለማምለጥ ስትል ሳውዲ ለቃ ወጥታለች። ትገደል! የሚሉ ጥሪዎች በማሕበራዊ ትስስር ድህረ ገጾች ከተሰሙ በኋላ ለህይወቷ በመስጋቷ ነው ከሳውዲ ለማምለጥ የወሰነችው።

በሱኒ ሳውዲ ቀንደኛ ጠላት በሺያ ኢራን ደግሞ ወጣቱ በማመጽ ላይ ነው። “ሞት ለአያቶላ ካሜኔይ! ሞት ለፍልስጤም!” በማለት በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ወጣት ኢራናውያን መንገድ ላይ እየወጡ ነው።

ስለእነዚህ ሁኔታዎች ዋናዎች የሚባሉት ሜዲያዎች ጸጥ ብለዋል፤ ስውዲም ኢራንም፤ ሁለቱም የፀረክርስቶስ አገራት የኢትዮጵያ ጠላቶች ናቸው። በእነዚህ ትዕቢተኞች፣ ግትር እብሪትኞች ላይ እየመጣባቸው ያለው መቅሰፍት ገና ብዙ ደም ያስለቅሳቸዋል።

በነገራችን ላይ በዛሬዋ ኢራን ወይም በቀድሞዋ ኃያሏ ፋርስ ላይ የእስልምና መቅሰፍት የመጣባት በ፮ኛው መቶ መጨረሻ ላይ በየመን የነበሩትን ክርስቲያን ኢትዮጵያውያን ጨፍጭፋ በመግደል የመንን ግዛቷ ባደረገቻት ማግስት ነበር። ይህ ብዙ የማይነገርለት ታላቅ የታሪክ ማስረጃ ነው!

ስለዚህ አስገራሚ ታሪክ ለአንዲት ክርስትናን ለተቀበለች ኢራናዊት አንድ ጊዜ ሳወሳላት፡ የተደሰተችው ደስታ አይረሳኝም፤ የክርስቶስን ብርኃን ስላየች ሁሉም ነገር ተገጣጠመላትና ነው።

እኛ ኢትዮጵያውያን እጆቻችንን ወደ እግዚአብሔር በመዘርጋት የአምላካችንን ድንቅ ሥራ እንታዘባለን።

ኡራኤልጊዮርጊስ ተክለ ሐይማኖት

______

 

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: