Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2018
    M T W T F S S
     123
    45678910
    11121314151617
    18192021222324
    252627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

የእሥራኤል ፖሊሶች ኢትዮጵያውያን መነኮሳትን በማንገላታቱ ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን ወደ ኢየሩሳሌም ማዛወሯን ለጊዜው ገታች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 13, 2018

በኢየሩሳሌም ከተማ፡ የኢትዮጰያውያን ርስት ወደ ሆነውና፡ የእስራኤል ሬድዮ ጣብያ ተከራይቶ ይሠራበት ወደነበረው ከ110ዓመት በላይ ያስቆጠረ ህንፃ የእስራኤል መከላክያ ሰራዊት በራሱ ፈቃድ ገብቶ አባቶችን በኃይል ማስወጣቱ፣ ማንገላታቱና ማሠሩ አንድ ተንኮል ከበስተጀርባው አለ ያስብላል።

የግብጽ እጅ፡ ወይስ ኢትዮጵያ በኢየሩሳሌም ጉዳይ ከጥቂት ወራት በፊት ባልተባበሩት መንግሥታት ከመሀመዳውያኑ ጋር በመሰለፏ?

ያም ሆነ ይህ፡ በአባይ ወንዝ ሳቢያ፡ እስራኤልም ሆነች አውሮፓ፡ ሁሉም ከግብጽ ጋር ማበሩን ይመርጣሉ።100 ሚሊየን ቁንጥንጥ ግብጻውያን ከሚጠሙና ከሚራቡ 100 ሚሊየን ሰላማዊ ኢትዮጵያውያን መቸገራቸውን ይመርጣሉ። 100 ሚሊየን የተራቡ ግብጻውያን እስራኤልንም ሆነ አውሮፓን በስደትና በሽብር ያተረማምሷቸዋልና።

ስለዚህ፡ ዓለማዊው የእስራኤል መንግስት ኢትዮጵያን ወደ አረቦቹ በይበልጥ እንድትጠጋ መግፋት፣ ከእስራኤል ጋር ያላትንም ቅርርብ በጣም እንዳታጠብቅና በረከቱንም እንድታጣ ይሻሉ። የአባቶቻችንም መንገላታት የሚነግረን፡ ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን ወደ ኢየሩሳሌም አዙራ፡ በእስራኢል ዘንድ መልካም ግምት እንዳይሰጣት ለማድረግ በማሰብ ሊሆን ይችላል። Problem – Reaction – Solution.

ለማንኛውም፡ እስራኤል ዕብራይስጥ ቋንቋን እንደ አረብኛ ከቀኝ ወደ ግራ መጻፉን ማቆም አለባት፤ ኢትዮጵያም ከአረቦች ጋር ጢብጢብ መጫዋቱን መተው ይኖርባታል።

[ትንቢተ አሞጽ ፱፥፯]

የእስራኤል ልጆች ሆይ እናንተ ለእኔ እንደኢትዮጵያ ልጆች አይደላችሁምን? ይላል እግዚአብሔር

______

 

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: