Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2018
    M T W T F S S
     123
    45678910
    11121314151617
    18192021222324
    252627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

የረመዳን ጋኔን | በ አርባ ምንጭ ሀይቅ አጥማቂው ጴንጤ ፓስተር በአዞ ተገደሉ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 6, 2018

አስቃቂ ነው፤ ነፍሳቸውን ይማርላቸው!

ቢቢሲ እንደዘገበው

በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ በላንቴ ቀበሌ ልዩ ስሙ መርከብ ጣቢያበተባለ ስፍራ ከሀይቅ ዳር ቆመው መንፈሳዊ አገልግሎት በመስጠት ላይ የነበሩ ፓስተር በአዞ በደረሰባቸው ድንገተኛ ጥቃት ህይወታቸው ማለፉን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የወረዳው ፖሊስ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ፓስተር ዶጮ እሸቴ የተባሉት የሃይማኖት አባት እሁድ ጠዋት 2 ሠዓት ተኩል አካባቢ ቁጥራቸው በግምት ሰማኒያ አካባቢ የሆኑ ተከታዮቻቸውን በሃይቁ ውሃ እያጠመቁ በነበረበት ሰዓት አደጋው እንደደረሰባቸው አቶ ከተማ ካይሮ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

አቶ ከተማ ስለ ክስተቱ ሲያስረዱ አጥማቂው የመጀመሪያውን ሰው አጥምቀው ሁለተኛውን ማጥመቅ ሲጀምሩ አዞው በድንገት በመውጣት የሚጠመቀውን ሰው ገፍትሮ ሲጥለው አጥማቂውን ግን ጎትቶ ወደ ውሃው ይዞት ሄዷልብለዋል።

የወረዳው ፖሊስ ባልደረባ የሆኑት ዋና ሳጅን እውነቱ ካንኮ በበኩላቸው ክስቱት መፈጠሩን አረጋግጠው፤ በወቅቱ በአካባቢው የነበሩ ዓሳ አስጋሪዎችና ወጣቶች በአዞው ጥቃት የተፈፀመባቸውን ግለሰብ ከአዞው ለማስጣል ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ እንደቀረ ተናግረዋል።

ዋና ሳጅን እውነቱ ምንም እንኳን የፓስተሩን ህይወት ማዳን ባይቻልም የአካባቢው ማህበረሰብ የሟች አስከሬን ከአዞው ለማስጠል እንደተቻለ ጨምረው አስረድተዋል።

የሟቹ ፓስተር ዶጮ እሸቴ የቀብር ሥነሥርዓትም ሰኞ እለት ተፈፅሟል።

______

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: