Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • May 2018
    M T W T F S S
     123456
    78910111213
    14151617181920
    21222324252627
    28293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for May 10th, 2018

እህተ ማርያም | ዶ/ር ወይም “Dr.“ የሚባለውን የማዕረግ ስም የሚሰጡት የወደቁት መላእክት ናቸው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 10, 2018

ትክክል ናት እህታችን፡ እያየነው እኮ ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘ እኔ በግሌ ያየኋቸው ወይም የታዘብኳቸው አንዳንድ ነገሮች አሉ። የዶክትሬት ቆብ ማድረግና ከረባት ማሰር ሁሌ ይከነክነኛል። የ ዶ/ር ማዕረግ ከአውሬው ምልክቶች አንዱ ነው፤ በክርስቲያናዊው የመንፈሳዊ ሕይወታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠምቀን የክርስትና ስም፡ ብሎም ቅብዓቅዱሱን ተቀብተን የሊቅነቱ ማዕረግ እንደሚሰጠን፡ በፀረክርስቶሱ ዓለምም እንዲሁ ዶክትሬቱን ለመቀበል የአውሬውን ቅባት “በመቀባት” እርሱ የፈጠረውን ሥርዓት ለማገልገል ቃል በመግባት ነው፤ ነፍስን በመሸጥ። በተለይ በውጭ አገራት ዶክትሬቱን የተቀበሉ ወገኖች ማዕረጉን ከተቀበሉ በኋላ ለለገሰቻቸው አገር እድሜ ልካቸውን ጠበቃ መቆም ወይም የአገሪቷን ፍላጎቶች የማሟላት ግዴታ አለባቸው። ባጠቃላይ፡ የባዕዳን መጠቀሚያ በመሆን ከሀገራቸው ጥቅሞች በተጻራሪ ይቆማሉ።

ለምሳሌ፡ በእምነት በኩል ፕሮቴስታንቶች ለ አሜሪካና አውሮፓ፣ ካቶሊኮች ለጣልያን፣ ሙስሊሞች ለሳዑዲ አረቢያ ሲሉ ከማንነታቸውና ከገዛ ሀገራቸው ጥቅም በተጻራሪ እንዲንቀሳቀሱ ሲደረጉ፤ በዶክትሬት የተካኑትም ወገኖች፡ ምዕራባውያኑ “ዲሞክራሲ” “ኒዖ ሊበራሊዝም፣ ወይም “ሊበራል ዲሞክራሲ” ለሚሉት የማታለያ ርዕዮተ ዓለም እንዲታገሉ ይገደዳሉ።

በጥቂቱም ቢሆን ቢዲዮው ላይ፡ ዶ/ር አስፋ ወሰን አስራተ እና ዶ/ር ደረሰ ጌታቸው ለዚህ ኃይለኛ መልዕክት እንደ ምስክር ሆነው ቀርበዋል።

ሁሉም ከተቀበረባቸው የዶክትሬት መርዝ እንዲፀዱ እግዚአብሔር ይርዳቸው፡ ይርዳን።

______

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: