የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች፡ በጀርመኗ ሙኒክ ከተማ፡ ቤተክርስቲያናቸው አጠገብ ቆመው ጸሎት ሲያደርሱ፡ ዘረኞቹ ፎቶ በማንሳት፡ መጀመሪያ ፊስ ቡክ ላይ ለቀቁት፡ ከዚያም በይቦታው ወሬውን አሠራጭተው ብዙ ነጮች እንዲቆጡ ለማድረግ በቅተው ነበር።
“ተመልከቱ! አዲስ መጤ ጥቁሮች ቤተክርስቲያናችን ላይ እየሸኑ ነው!”
በማለት ብዙ የጥላቻ እና የዛቻ ዘመቻ በኢትዮጵያውያኑ (ኤርትራ) ላይ ለመቀስቀስ ሞክረዋል።
ጸሎት እያደረሱ እንደሆነ ከጀርመን ካቶሊክ ቤተክርስቲያን በኩል ማስተባበያ ቢሰጥም አምነው መቀበል ስላቃታቸው/ስላልፈለጉ እጅግ የሚያሳዝን የጥላቻ መርዛቸውን መርጨቱን ቀጥለው ነበር።
በጣም አሳዛኝ ሁኔታ ነው፤ በጣም አሳዛኝ ሰዎች ናቸው። ጀርመናውያኑ እራሳቸው ከፈጠሩት ውድቀታቸው ምናልባት ኢትዮጵያውያኑ እንደ መልአክ ተልከውላቸው ሊሆን ይችላል፣ ግን ወደ ጨለማው በመግባታቸው በጎ ነገር መሻትና ጥሩውን ከመጥፎ ለመለየት ተስኗቸዋል። ለልጆቹ ወደፊት ማሰብ ያቃተው ትውልድ ምንም የሚያኮራ ነገር ሊኖረው አይችልም።
እንደ ነቀርሳ እየበዘበዟቸው፣ እየበደሏቸው፣ ህፃናቶቻቸውን እየደፈሩባቸው ብሎም እየገደሉባቸው ባሉት በሙስሊሞቹ ወራሪዎች ላይ “የለም የገነባነውን ማፍረስና ማስፈረስ የለብንም!“ በማለት እንደ መነሳሳት፣ ምንም ባላደረጓቸው፡ ምናልባትም ሊረዷቸውና ሊጠቅሟቸው በሚችሉት የኢትዮጵያ (ኤርትራ) ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ላይ ያላግባብ አካኪ ዘራፍ ይላሉ።
ዘረኞች፡
ግብዞች! ደካሞች! ተልካሾች! ውዳቂዎች!