Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • May 2015
    M T W T F S S
     123
    45678910
    11121314151617
    18192021222324
    25262728293031
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

ከእስልምና ጨለማ የወጣው ወንድማችን በ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የገጠመው ፈተና

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 1, 2015

አዲስ አበባ ኃሙስ ዕለት ቀትር ልክ ከቀኑ ስድስት ሰዓት፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን።

ቀትር የፀሐይ ብርሃን ከማንኛውም ሰዓት በበለጠ የሚደምቅበት እና ፀሐይ በራሳችን ትክክል የምትሆንበት ሰዓት ነው። በቀትር በራስ ጥላ ምክኒያት እንኳ ጨለማ የለም። እነሆ ፀሐይ ጽድቅ እግዚአብሔር ያለ ምንም ግርዶሽ በሚያበራበት፡ የኃጢአት ጨላማ ገና ባላወቃት በኤደን ገነት ውስጥ በቀትርሆነው ወላጆቻችን ነፍሳችን የወደደችው አንተ ንገረን፡ ወዴት ታስማራላህ? እዘዘን፡ ትእዛዝህን በደስታ እንፈጽማለንይሉት ነበር። ነገር ግን ፈጣሪ እግዚአብሔርን የምትወድን ነፍስ ከክብሯ ለማዋረድ፡ ከፍቅሯ ለማብረድ ቀን ተሌት የሚደክመው ጠላት ዲያብሎስ ለአምላካቸው በፍቅር እና በእውነት ይታዘዙባት ከነበረች ቀትርከተባለች የገነት ኑሮአቸው አውጥቶ ወደ ጨለማ እና የሞት ጥላአወረዳቸው፡ ለመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነየተባለው ወልድ ከልጅ ልጃቸው ተወልዶ እስኪያድናቸው ድረስ። ]ፊልጵ. ፪ ፥ ፰}

አበ ብዙኃን አብርሃም እንደ ቀትር ፀሐይ የሚንቦገበግ አምልኮተ እግዚአብሔር በምድር ሰውነቱ ባየ ጊዜ ርስት አድርጎ ሊቀበለው ወዳለው ሥፍራ ለመውጣት በእምነት ታዘዘ፤ ወዴትም እንደሚሄድ ሳያውቅ ወጣ” (ዕብ. ፲፩፥፰)። በዚህ ጊዜ ዘመዶቹን፡ አገሩን እና የአባቱን ቤት ትቶ የሚወድደውን እግዚአብሔርን ይታዘዝ ዘንድ የወጣ የአባታችን የአብርሃም ነፍስ ነፍሴ የወደደችህ ፈጣሪዬ አንተ ንገረኝ፡ ወዴት ትመሰጋለህ? ብቻ አንተ እረኛዬ የምትሆን ከሆነ ያደግሁበትን አገር ለቅቄ እንደ በግ እከተልሃለሁ፡ በድንኳንም ቢሆን እኖራለሁእያለች ነበር።

እረኛው እግዚአብሔር መለሰ። በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት።እግዚአብሔርም አለ፦ እኔ የማደርገውን ከአብርሃም እሰውራለሁን? አብርሃም በእውነት ታላቅና ብርቱ ሕዝብ ይሆናልና፡ የምድርም አሕዛብ ሁሉ በእርሱ ይባረካልና” (ዘፍ. ፲፰፥፩)

ይህ ቪዲዮው ላይ የሚታየው ወንድማችን ቀትር ላይ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ቦታ ላይ ለረጅም ጊዜ ተመበርክኮ ጸሎቱን በጩኸት ለፈጣሪ ያደርሳል። አብዛኛውን ሁኔታ ቪዲዮው ውስጥ አላስገባሁትም እንጂ ያጋጣሚ ሆኖ የልጁን ሁኔታ ትንሽ ራቅ ብዬ በጥሞና እከታተል ነበር። ልጁም፡ ጎርጊስ፡ የት አለህ? ና እንጂ?….ኧረ ጎርጊስ…..ኧረ ጎርጊስ….ና እንጂየት አለህ?” በማለት እጆቹን ወዲያ ወዲህ እያወዛወዘና እየተንጠራራ ያለማቋረጥ ይጮህ ነበር። በመሃልም፡ የእስላሞችን አምላክ እየጠራ አላህ ወአክበር! አላህ ወአክበር!” በማለት ሲጮህ የሰሙ ምዕመናያን፡ ቪዲዮው ላይ እንደሚታየው ጠጋ በማለት፡ ምንድን ነው ነገሩ፡ ይህ ቤተ ክርስቲያን ነው፡ አላህን ከፈለግክ ውጣ እና ወደ መስጊድ ሂድይሉታል።

እኔም በበኩሌ ይህ ወንድማችን ለምን ቤተክርስቲያን መጥቶ የሌላ አምላክ ስም ይጠራል? በማለት ከቤተክርስቲያን ሊወጣ ሲዘጋጅ በትህትና ጠየቅኩት። ወንድማችን በቅርቡ ከእስልምና ወጥቶ ወደ ክርስትና እንደገባ በጥቂቱ አወሳኝ። ቀጥዬም እግዚአብሔር መንገዱን ይምራህ፡ ለተቀሩት ሙስሊም ወገኖቻችንንም ጌታችን ክርስቶስ ከጨለማ አውጥቶ ብርሃኑን ያሳያቸው። እንደ አብርሃምም በትህትና የሚማጸኑ ከሆነ እግዚአብሔር አምላካችን ይገለጥላቸዋል፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ይርዳቸውበማለት ተሰናበትኩት።

__ 

Leave a comment