Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • November 2014
    M T W T F S S
     12
    3456789
    10111213141516
    17181920212223
    24252627282930
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for November 21st, 2014

የኅዳር ሚካኤል — ብሩክ ዓመት በዓል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 21, 2014

ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነትከሚለው የንቡረ እድ ኤርምያስ ከበደ ወልደየሱስ መጽሐፍ የተወሰደ

ከከበረ ሰላምታ ጋር

የኅዳር ሚካኤልተብሎ በኅዳር ፲፪ ቀን የሚከበረው የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በዓል ነው።

እግዚአብሔር፡ የእሥራኤልን ሕዝብ በሙሴ አማካይነት ከፈርዖን የባርነት አገዛዝና ከምድረ ግብፅ የሥቃይ ኑሮ ነጻ አውጥቶ መዓልቱን በደመና ሌሊቱንም በእሳት ዓምድ ከልሎ እየመራቸው የቀይ ባሕርንም በደረቅ ምድር አሻግሮ እየጠበቃቸው፡ ውኃውን ከዓለት አፍልቆ ኅብስተ መናውን ከሰማይ አውርዶ፡ ሥጋ አማረንቢሉም ድርጭቱን በነፋስ አዝንሞ እየመገባቸው እንደተንከባከባቸው ይታወቃል፡ በአምላካቸው ቸርነት ይደረግላቸው የነበረውን ያን ኹሉ የተራዳዒነት ተልእኮ ይፈጽምላቸው የነበረው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ነበር። ይኹን እንጂ እነርሱ ለዚህ ኹሉ አምላካዊ ቸርነት ውለታቢሶች በመኾን ፈጣሪያቸውን አሳዘኑ፡ ይኸውም ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር ለመገናኘት ወደተራራ ወጥቶ ለጥቂት ቀናት በሱባዔ መቆየቱን ምክንያት አድርገው፡ ካህን ወንድሙን አሮንን በፊታችን የምናስቀድመው ጣዖት ካልሠራህልንብለው አስጨንቀው ጣዖቱን ማሠራታቸውና ማምለካቸው ነው።

እነርሱ ሊጠፉበት የነበረውን የእግዚአብሔርን ቍጣ፡ ሙሴ በማለሟልነቱ አማልዶ ቢያስመልሳቸውም የእነርሱ ማለትም የእሥራኤል ልጆች ፍላጎት፡ እንደ ኢትዮጵያ ልጆች፡ እግዚአብሔርን በእውነትና በመንፈስ ማምለክ ሳይኾን እንደአሕዛብ በሚታይና በሚዳሰስ ግዙፍ ነገር መኾኑን እግዚአብሔር ተመለከተ፡ እንዲህ ከኾነ ብሎም እርሱ እግዚአብሔር ቃሉን በጽላት ላይ ቀርፆ ያንም ጽላት በግእዝ ታቦትበሚባለው ሣጥን ውስጥ እንዲያስቀምጡት አዝዞ፡ በዚያ እንዲያመልኩት ታቦተ ጽዮንየተባለችውን ያቃል ኪዳን ምስክር ሰጣቸው። ከዚህ የተነሣ ጠላቶቻቸውን ድል ይነሡባት ዘንድ እንዲህ አድርጎ በሰጣቸው እርሱ ለእነርሱ በሚገልጽባት እነርሱም እርሱን በሚያመልኩባት በዚችው የጽላት ሕግ ሃይማኖትና ምግባር ጸንተው ይኼዱ ወይም አይኼዱ እንደኾነ ሊፈትናቸው አርባ ዓመታት ሙሉ በምድረ በዳ አንከራተታቸው። በዚያን ጊዜ ለእሥራኤል ሕዝብ አንተ አንገተ ደንዳና ሕዝብ ስለኾንህ፡ በመንገድ ላይ እንዳላጠፋህ እኔ በአንተ መካከል አልወጣምና በፊትህ መልአኬን እሰድዳለሁ!” ብሎ የመደበላቸው መልአክ፡ ቅዱስ ሚካኤል ነበረ። ይህ ኹሉ ዝክረ ነገር በኦሪት ዘጸአት መጽሓፍ ውስጥ ተመዝግቦ፡ ዛሬ ድረስ እንደሚነበብ ታውቃላችሁ።

በዚያን ዘመን እግዚአብሔር ለወዳጆቹ ለአብርሃም ለይስሓቅና ለያዕቆብ የገባውን ቃል ኪዳን በማሰብ ለእሥራኤል ልጆች ያን የመሰለ ታዳጊነቱን በመልአኩ በቅዱስ ሚካኤል አገልጋይነት ያደርግ እንደነበረ፡ ዛሬ እውነተኞቹ እሥራኤል እኛ ስለኾንን ይህንኑ ተራዳኢነቱን ይፈጽምልናል!” ብለው የኢትዮጵያ ልጆች የቅዱስ ሚካኤልን በዓል፡ በዚህ ዕለት ያከብራሉ።

በአገራችን በኢትዮጵያ በዚሁ በኅዳር ሚካኤል ዕለት ካህናቱ በየቤተ ክርስቲያኑ ጸሎተ ዕጣን እየደገሙ የማዕጠንት ዕጣን የሚያሳርጉት ሕዝቡ በከተማ ቍሻሻ የኾነውን ነገር ኹሉ እየሰበሰበ የሚያቃጥለው በገጠርም በየእርሻው በተለይም በቆላ የሚኖረው ወገን ስለወባና ወረርሽኝ በየመሬቱ ላይ እሳት አንድዶ ጪስ የሚያጨሰው ኅዳር ታጠነየሚባለውን ይትበሃል ለማስታወስ ነው፡ የዚህም ምክንያት በራእየ ዮሓንስ ተጽፎ እንደሚነበበው፡ ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይየሚባሉት መላእክት ስለዓለሙ ኹሉ ደኅንነት በሰማይ በጽርሐ አርያም የምስጋናና የልመና ጸሎትን ከዕጣን ማዕጠንት ጋር በእግዚአብሔር መንበር ፊት ያለማቋረጥ የሚያቀርቡትን ሥርዓት የተከተለ ነው፡ እንደዚሁ ኹሉ እኛንም እግዚአብሔር በምድር ላይ ካለፈው ዓመት ከማናቸውም ዓይነት ሕማምና ደዌ፡ ቸነፈርና በሽታ ጠብቆ ስላዳነን፡ ከሚመጣውም እንዲጠብቀን በማለት በዚያ ሰማያዊ ሥርዓት እኛም፡ ኢትዮጵያውያን ለፈጣሪያችን ምስጋናችንንና ልመናችንን ይኸው እናቀርባለን፡ በቅርቡ፡ በአጼ ምኒሊክ ዘመን ደርሶ የነበረውን፡ የኅዳር በሽታየሚባለውን ከመሰለ በዓመቱ ውስጥ ተላላፊ የሰውና የከብት በሽታ ገብቶ፡ ሊያደርስ ከሚችለው ጥፋትና ዕልቂት አድነንለማለት።

በዛሬው በኅዳር ፲፪ ዕለት፡ ፪ሺ፯ ዓ.ም፡ ፲፫ ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ህጻናት የልጅነት ልምሻ / ፖሊዮ ተላላፊ በሽታ መከላከያ ክትባት ይሰጣቸዋል። የዜናው ምንጭ አናዱሉ የተባለው የቱርክ የዜና ወኪል መሆኑ የሚገርም ነው። ይህችን ዕለት እናስታውስ! ኹሉን የሚያይ ቸሩ እግዚአብሔር ወገኖቻችንን / ልጆቻችንን ይጠብቅልን!

_

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

የቀድሞ ፌደራል ወኪል፦ “እነ ማይክል (ሚካኤል) ጃክሰን በሉሲፈራውያኑ ኢሉሚናቲ ነው የሚገደሉት”

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 21, 2014

በዚህ ቅዱስ በሆነው የሌቀ መላእክት፡ ቅዱስ ሚካኤል ዕለት፡ ይህን በጣም የሚገርም ቪዲዮ ስለ ሙዚቀኛው፡ ማይክልጃክሰን አማሟት የሚናገር ቪዲዮ ተመለከትኩ። ቪዲዮው ላይ የቀረቡትን አንዳንድ ሃሳቦች ሳዳምጥ፡ ተወዳጅ በሆኑ ዓለምዓቀፋዊ ሁኔታዎች ላይ፡ በተለይ ሙዚቃና እና ስፖርትን በተመለከቱ ነገሮች ላይ ጠለቅ አድርጌ እንዳስብ ተገደድኩ።

የሙዚቃ ሲዲበጣም ተወዳጅ በነበሩባቸው በ 1990ዎቹ ዓመታት፡ እኔም እንደ አብዛኛው ሰው ሲድዎቹን የመሰብሰብ ሆቢነበረኝ፤ በሞኝነት ዘመኔ፡ ወደ 2ሺህ የሚጠጉ ሲዲዎችን ለመሰብሰብ በቅቼ እስካሁን ድረስም ለማስታወሻ እና ለትዝብት አቆይቻቸዋለሁ። በጊዜው በጣም ተወዳጅ ናቸው የተባሉትን እንደ ማይክል ጃክሰን የመሳሰሉትን ዓለማቀፋዊ የሙዚቃ ከዋክብትአልጠላቸውም፡ ይህን ያህልም አልወዳቸውም ነበር። በጊዜው፡ ሰዎች ማይክል ጃክሰንየሚል ቅጽል ስም ቢሰጡኝም፡ የማይክል ጃክሰንን ሲዲ ፈጽሞ ገዝቼ አላውቅም። እንዲያው በተፈጥሮ በጣም ተወዳጅ ከሆኑ ነገሮች የመቆጠብ ባሕል አለኝና። አሁን እንደተረዳሁት፡ ዲያብሎስ፡ በጣም ማራኪና ተወዳጅ የሆኑትን ነገሮችና ሰዎች እየተከታተለ በእጁ እንደሚያስገባ ነው።

ይህን እይታዬን፡ ልክ ቪዲዮው ላይ እንደቀረበው ግለሰብ፡ ሌሎችም ይጋሩታል። ያለፈው የብራዚል የዓለም ዋንጫ፡ የመጀመሪያው የሰዶማውያን የዓለም ዋንጫ ነበር። ብዙዎቹ ቡድኖች የኢትዮጵያን ሰንደቃላማ ቅዱስ ቀለማትን ለመፃረር/ለማርከስ ከቀስተ ደመና የተወሰዱት የሰዶማውያን ኅብረቀለማት (ሰማያዊ፥ ቀይ፥ ቢጫ፥ አረንጓዴ) በብዙ ቡድኖች ዘንድ ይንጸባረቁ ነበር። በጊዜው እኝህ የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቄስ እዚህ ላይ ጠቁመው ነበር። ጨዋታዎቹ በሙሉ ማራኪ ያልነበሩ፥ ተጫዋቾቹም የተልፈሰፈሱና ደካማ ነበሩ። አዘጋጇ ብራዚል ባገሯ 7 ጎሎች ሲገባበትና ስትዋረድ ይህን ሰዶማዊ ልፍስፍስነት ነው ያንጸባረቀው። ተክኖሊጂ ተጠቅመው ይሆን? ሊሆን ይችላል፡ ሰይጣን በሚያስተዳድራት በዚህች ዓለማችን በድብቅ የማይፈጸም ነገር የለም።

RioChristRedeemerየብራዚሉ ዓለም ዋንጫ ከመጀመሩ ከጥቂት ወራት በፊት፡ የሪዮ ዲጀኔሮ ዋና መለያ የሆነው አንጋፋው የክርስቶስ ኃውልት በመብረቅ ተመትቶ ነበር(ማስጠንቀቂያ)። የአርጀንቲና እና ጀርመን ቡድኖች በመጨረሻ ሲጋጠሙና ጨዋታውም በቀጥታ በቴሌቪዥን ሲተላለፍ፡ ካሜራው ኃይለኛ የሆነውን የዚህን የክርስቶስ ኃውልት፡ ልክ ጀንበሯ ከበስተጀርባ ስትጠልቅ አሳየን(ሌላ ማስጠንቀቂያ)። የዓልም ዋንጫው ወሳጅ ለመሆን የበቃው የጀርመን ቡድን፡ ምናልባት 1/3ኛው ሰዶማዊ እንደሆነ – አሠልጣኙንና ረዳቶቹን ጨምሮ የጀርመን ጋዜጦች ይጽፉ ነበር።

ባጠቃላይ፡ ከሆሊውድ እና ከሙዚቃው ፋብሪካ ቀጥሎ፡ ዲያብሎስ ዓይኑን ያነጣጠረው ተወዳጅ በሆኑ የእስፖርት ዓይነቶች ላይ ነው። በጥቁር ተጨዋቾች የበላይነት ለዘመናት ሲካሄዱ የነበሩትና፡ ተወዳጅ የሆኑትም የNBA ቅርጫት ኳስ ፍረንቻይዞች አንድበአንድ በዘረኞቹ እና በሰዶማውያኑ እጅ በመውደቅ ላይ ይገኛሉ።

ሙዚቃውን በሚመለከት፡ በሉሲፈራውያኑ እጅ የገባው የሙዚቃው ኢንዱስትሪ በጣም ኃይለኛ የሆኑትን የጥቁር አሜሪካውያን የ ብሉውስ እና ጃዝዘርፎች ተወዳጅ እንዳይሆኑ ቶሎ በመቅጨት፡ ሰውየው ቪዲዮው ላይ እንደሚናገረው፡ ራፕ እና ሂፕሆፕን በመላው አለም ተቀባይነት እንዲያገኙ አደረገ። ችሎታ ያለውም ቃላት ደርዳሪ፡ በመጠጥ፣ እጽ እና ወሲብ ላይ ትኩረት አድርጎ በአጭር ጊዜ ብዙ ገንዘብ እንዲሰበስብና ዝናንም እንዲያተርፍ ተፈቀደለት። ልክ፡ ጥቁሩንፕሬዚደንት ኦባማን ሥልጣን ላይ በማውጣት ሰላማዊና ኃይለኛ የነበረውን የጥቁሩን የጸረዘረኝነት እንቅስቃሴ ለመቅጨት እንደቻሉት፡ ጥቁሩ በሠለጠነ መልክ የበላይነትን በሚያሳይባቸው በሙዚቃ፣ ስፖርትና ወዘት. ቦታዎች ሁሉ መርዛቸውን ይረጫሉ። ሌላ ምሳሌ፡ በፈርግሰን፡ ሚዞሪ፡ የተበደሉት ጥቁሮች የዘረኝነት ተቃውሞቻቸውን ለማሰማት ወደ አደባባይ ሲወጡ፡ ትግላቸውን ይነጥቋቸው ዘንድ ከእነርሱ ጋር አብረው የሚሰለፉ አክራሪ እስላሞች ይልኩባቸዋል። ይህም የሚያሳያን፡ ልክ በመላው ዓለም እንደሚታየው፡ በአሁን ሰዓት የሉሲፈራውያኑ ዋና መሣሪያዎች ሰዶማውያን እና ሙስሊሞች መሆናቸውን ነው። እራሳቸው ጥቃት እየፈጸሙና ሌሎችን እየበደሉ እንደ ተበዳይ መብታችን ይጠበቅ!” እያሉ በመላው ዓለም የሚጮሁት እነዚህ ሁለት አረማዊቡድኖች ናቸው። በነገራችን ላይ፡ ፕሬዚደንት ኦባማ (ኦክላሆማ ጋር ይመሳሰላል) የኢሚግሬሽኑን ጉድይ በሚመለከት ለስደተኞች የመቆያ ፈቃድ ለመስጠት መወሰናቸው፡ በድብቅ ያስገቧቸውን ሙስሊም ወንድምቻቸውን ለመርዳት በማሰብ ነው። የዛሬው ንግግራቸው በጣም ያሳፍር ነበር፤ እኚህ ሰው ፕሬዚደንት ለመሆን መብቃታቸው የሚገርም ነው።

ወደ ኢትዮጵያ ብንመጣም፡ ድሆቹኢትዮጵያውያን አትሌቶች በየውድድሩ የበላይነት መያዛቸውን ያልወደዱት ሉሲፈራውያን በአንድ በኩል፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ የአጭር ጊዜ ድል ሊቀዳጁ በሚችሉ ኤጀንቶቻቸው ሥር እንዲወድቅ፡ ብሎም ከጎረቤት አገራት (ሶማሊያ፣ ሱዳን እና ኬኒያ ) የመጡ አትሌቶችን እያበረታቱ ኢትዮጵያውያኑን እንዲያዋርዱ ያደርጋሉ። በሌላ በኩል ደግሞ፡ አትሌቲክስ በመላው ዓለም ተወዳጅነት እንዲያጣ የመገናኛ ብዙኃንን አትኩሮት እንዳያገኝ፡ ተመልካቾች ወደ ስቴዲየሞች እንዳይሄዱ ስውር የሆነውን ሥራቸውን ይሠራሉ። ለአትሌቲክስ ወደ ስቴዲየም ከሚሄደው ተመልካች የ ዳርት ስፖርትንለማየት የሚሄደው ይበዛል። በየከተሞቹ የሚካሄዱት የማራቶን ሩጫዎች እስካሁን ተወዳጆች ናቸው፤ ሆኖም ይህንንም እየተተናኮሉት ነው፤ የቦስተኑ ማራቶን በእስላም ሽብርተኞች መጠቃቱ እንደ ምሳሌ ይወሰዳል። ለመሆኑ ፊሊፖስየተባለው ትውልደኢትዮጵያዊ በቦስተኑ ጥቃት ምን ዓይነት ሚና ይጫወት ይሆን? ሌሎች ምሳሌዎች፡ ዳይመንድ ሊግየሚባለውን ውድድር ክፍያ ለሚጠይቁ የኬብል ቴሌቪዥን ጣቢያዎች በመስጠት ብዙኃን ተመልካቾች እንዳያዩት መደረጉ፣ ዋና ዋና የሆኑትን ዓለም ዓቀፍ ውድድሮች እንደ ካታር ለመሳሰሉት የሉሲፈራውያኑ አገሮች መሰጠቱ፡ በዚህ አጋጣሚ የሚጠቀሱ ናቸው። የሚቀጥለው የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ በሩሲያ እንዲካሄድ ሲወሰን፡ ሩሲያ የሉሲፈራውያኑን ማሕበረሰብ ትቀላቀላለች፡ ጸረሰዶማውያን የሆነውንም ባሕሏንም ትተዋለች የሚል እምነት ስለነበራቸው ነበር፤ ነገር ግን ይህ ስላልሆነ የዩክሬንን ጦርነት በመቀስቀስና የተለያዩ ማዕቀቦችን በመጣል ኦርቶዶክስ ሩሲያን ሊይንበረክኩ ሲታገሉ ይታያሉ።

በአገራችንም ተመሳሳይ የሆነ ጸጥተኛ ጦርነት በሁሉም መስክ በመካሄድ ላይ ነው። ባሕሉን ሃይማኖቱን፤ አየሩን፥ ምግቡንና ውሃውን ለመበከል የሚካሄድ ጦርነት አለ። ሙዚቃን በሚመለከት፡ ሌላውን ትቼ አንድ ምሳሌ ልስጥ፤ ይኽውም፡ አንድ አብነት አጎናፍርየተባለ ዘፋኝ አለ። ይህ ዘፋኝ፤ ምንም ጥርጥር የለውም፡ ጥሩ ቾሎታና ብቃት ያለው ሙዚቀኛ ነው። ነገር ግን ይህን ብቃቱን በጣም አደገኛ ሆኖ ነው ያገኘሁት። ምክኒያቱም፡ የዜማ አወራረዱ ያሬዳዊ የሆነውን የኢትዮጵያ ዜማ ስለሚጻረርና ጋኔናዊ በሆነው የአረብ ዜማ ስለሚሸፈን ነው። በአረብና የአረብ ሳተላይት ቴሌቪዥን ያነጣጠረበት ሕዝባችን ቀስበቀስ እየደነዘዘ ጋኔናዊ ዜማውንም እየወደደ መጥቶ ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን ይህን መሰሉ ጉዳይ ቶሎ በጋሻ ካልተመከተ አሁን የሚታየውን የስነምግባራዊ ድህነት በይበልጥ ያስከፋዋል። ዝም ብለን እንዲሁ በቀላሉ አንየው! ባሕል፥ ቋንቋና እምነት ቀስበቀስ ነው የሚሸረሸረው። የወንድም አብነት አጎናፍርን ዓይን ልብ ብለን እንመልከት፤ ይህን በደንብ ይሳያናል። (ይቅርታ፡ ወንድም ዓለም!)

ለመሆኑ የኢትዮጵያ ባሕል፣ ሃይማኖት ወይም ሙዚቃ ጎረቤት በሆኑት የአረብ እና የአፍሪቃ አገራት ተቀባይነት አለውን? የለውም! ጭራሹንም የማይታሰብ ነው! መቼም ፈረንጅ ሁሉንም መሞከር ስለሚወድ አንዳንዴ ጎበዝየሚያስብለው ነው፡ ግን እስኪ የ ሃበሻልብስ የሚለብስ አርብ ወይም አፍሪቃዊ እንፈልግ፤ የትም አናገኝም፤ ከሺህ ዓመት ግኑኝነት በኋላ ለባህላችን ባዕድ ሆነው ነው? አይደለም! ነገሩ መንፈሳዊ መንስኤ አለው፤ እነርሱ ማን ምን እንደሆነ አውቀውታል። እኛስ? እድሜ ለሉሲፈራውያኑ፡ ማንነታችንን ሆነ የሌላውንም ማወቅ ተስኖናል። ይህ ነው ድኽነትማለት። እንግዲህ በይበልጥ የዳበረውና የተራቀቀው የኛው ሆኖ እያለ ለምንድን ነው የሉሲፈራውያኑን ቆሻሻ ለመቀበል የምንቁነጠነጠው? ቆንጠጥ ብለን እናስብበት!

ለማንኛውም የአሜሪካ መከላከያ ምኒስቴርን ለ20 ዓመት ያህል አገልግያለሁ የሚለውን ግለሰብ ስናዳምጥ፤ ጥቁር አሜሪካውያንን ለመቆጣጠር የሙዚቃው ፋብሪካ አመቺ ተቋም ነው። እነ ቱፓክ ሻኩርና ማይክል ጃክሰንም በመንግሥት እጅ ነው የተገደሉት ይለናል። ማይክል ከመሞቱ ከጥቂት ሰዓታት በፊት በስልክ ያስተላለፈውን መልዕክት አቅርቦልናል፡ የሥራ ባልደረቦቹም እስከ መጪው ሰኞ ይህን በተመለከት እንደርሱ የማይወጡ ከሆነ፡ ምስጢራቸውን ሙሉበሙሉ እንደሚያጋልጥ ቃል ይገባል። የሰኞ ሰው ይበለን!

__

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith, Infotainment | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: