Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • January 2014
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    2728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for January 6th, 2014

ብሩክ ገና – Merry Christmas

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 6, 2014

እንኳን ለብርኃነ ልደቱ በሰላም አደረሰን!

የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት (ልደተ እግዚእነ) በማስመልከት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ያስተላለፉት መልዕክት፦

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን!

–በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ

–ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ

–የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረኡ የቆማችሁ

–በሕመም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችሁ

–እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ፣

ወልድ ተብሎ ውሉድ እንድንባል ላበቃን ለጌታችን ለአምካችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት እንኳን በሰላም አደረሳችሁ!

ወናሁ ትፀንሲ ወትወልዲ ወልደ ወትሰም ስሞ ኢየሱስ ዘውእቱ ያድኀኖሙ ለሕዝቡ እምኃጢአቶሙ፤ እነሆ ትፀንሻለሽ፣ ወንድ ልጅንም ትወልጃለሽ፣ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና፣ ስሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ” {ሉቃ1 31 ፤ ማቴ 1 21]

ሁላችንም እንደምናውቀው፤ ዘላለማዊና ቀዳማዊ የሆነ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ሰው ሆኖ እንዲወለድ ምክንያት የሆነው፣ የሰው ኃጢአት ነው።

ሰው በኃጢአት ምክንያት ከእግዚአብሔር ተለይቶ ክብሩን ካጣ በኋላ፣ በነፍሱም ሆነ በሥጋው፣ ለአጠቃላይ ውድቀት ተዳረገ፤ ንጹሕ የነበረ ባህርዩ እንደ ሰኔና እንደ ሐምሌ ጎርፍ ደፈረሰ፤ የኃጢአት ድፍርሱም እየባሰና እየከፋ ከመሄድ በቀር፣ መሻሻል አላሳየም፤ ይሁንና የክብር አምላክ የሆነ እግዚአብሔር አምላካችን፣ ለክብር በክብር የፈጠረውን የሰው ልጅ፣ እንደ ወደቀ ሊቀር አልፈለገምና፣ የመዳኛ ዘዴ አበጀለት።

አምላካችን እግዚአብሔር ሰውን የማዳን ሥራው፦

  • መቼ?
  • በማን?
  • የት?
  • እንዴት?

እንደሚከናወን፣ አምስት ሺሕ አምስት መቶ ዘመን ሙሉ በትንቢት፣ በምሳሌ፣ በራእይና በቀመረ ሲባኤ፣ በቅዱሳን ነቢያቱ አማካኝነት፣ ለዓለም ሲገልጽ ቆየ።

በእርሱ የተያዘው ቀጠሮ ሲደርስ፣ በፊቱ የሚቆመውን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን፤ ወደ ድንግል ማርያም ላከ። ቅዱስ ገብርኤልም፣ ከእግዚአብሔር ንገር ተብሎ የተላከበትን መልእክት ይዞ፣ ወደ ድንግል ማርያም መጣ፤ እንዲህም አላት፡ እነሆ ትፀንሻለሽ፤ ወንድ ልጅንም ትወልጃለሽ፤ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና፣ ስሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ፤ እርሱ የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ይባላል፤ አላት።

ከዚህ አገላለጽ በመነሣት፣ ፍሬ ነገሩን ስናስተውል፣ ከቅድስት ድንግል ማርያም የሚወለደው ሕጻን፦

  • ዕሩቅ ብእሲ (ተራ ሰው) ሳይሆን፣ የእግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር መሆኑን
  • የስሙ ትርጓሜም መድኃኒት ማለት መሆኑን
  • መድኃኒትነቱም ለሕዝቡ ሁሉ መሆኑን
  • ሕዝቡን የሚያድናቸውም ከኃጢአታቸው መሆኑን

በማያሻማ ሁኔታ ማወቅ ይቻላል።

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቼ፣ ምእመናንና ምእመናት

ethiopian_mary_jesus_sallaway_8603የጌታችን መድኃኒትነት ድንበር የለሽና፣ በሁሉም በሽታዎች ላይ የሚሠራ ቢሆንም፣ በዋናነ ግን፣ በትልቁ የኃጢአት በሽታ ላይ ያነጣጠረ መድኃኒት መሆኑን፣ በተጠቀሰው ኃይለ ቃል መረዳት ይቻላል። ምክንያቱም በዓለም ላይ የሚታየውን ክፉ በሽታ ሁሉ፣ ሰበብ በመሆን ጎትቶ ያመጣብን ይህ ኃጢአት ነውና፣ ጌታችን በዋናነት እርሱን ለመደምሰስ መምጣቱን ለማሳየት፣ ከኃጢአታቸው ያድናቸዋል ተብሎ በግልጽ ተለይቶ ተነገረ፤ በሽታው ትልቅ መሆኑን የምንረዳው፣ ትልቅ ዋጋ ያለው መድኃኒት፤ ያውም የእግዚአብሔር ልጅን ያህል፣ ለመሥዋዕትነት ያስፈለገው በመሆኑ ነው።

ለመሆኑ የኃጢአት በሽታ የሚያስከትለው ጉዳት ምንድን ነው? ያልን እንደሆነ፤ ሰውን ከእግዚአብሔር በማራቅና እግዚአብሔርን በማሳጣት፣ ሰውን ማዋረድ፣ ማጎሳቆልና መግደል ነው፤

ሰው እግዚአብሔርን ካጣ፣ ሁሉንም ያጣል፣ አዳም አባታችንና ሔዋን እናታችን ያጡም ይህንን ታላቅ ሀብት ነበር፤ እግዚአብሔርን ሲያጡ፤ ሁሉንም አጡ፤ ኃጢአተኞችም ሆኑ፤ ኃጢአተኛ ማለት ያጣ፣ የነጣ ማለት ነው፤ ምንን ያጣ? እግዚአብሔርንና የእግዚአብሔር የሆነውን ሁሉ ያጣ ማለት ነው፤

ሰው ከእግዚአብሔር ከተለየ፦

  • ሕይወት የለም
  • ሰላምም የለም
  • ክብርም የለም

በአጠቃላይ መልካም የሆነ ነገር ሁሉ የለም፤ ሊኖር የሚችለው ተቃራኒው ነው፤ እርሱም፦

  • ሞት
  • በሽታ
  • ድህነት
  • ጠብ
  • መለያየት
  • ውርደት

የመሳሰለው ክፉ ነገር ሁሉ ነው ሊኖር የሚችለው፤

ከዚህ አንጻር ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ፣ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋል ሲባል፣ በዋነኛነት እግዚአብሔርንና የእግዚአብሔር የሆነውን ሁሉ ከማጣት ያድናቸዋል ማለት ነው።

__

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

Ethiopians Challenged — The Middle East Tested

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 6, 2014

All you inhabitants of the world, and dwellers on the earth, see, when he lifts up a banner on the mountains; and when he blows a trumpet, hear.” [Isaiah 18:3]

30,000 African Migrants Take to Tel-Aviv Streets Protesting Detention Policy

30Tens of thousands of Africans took to the streets of Tel Aviv on Sunday in protest of Israel’s detention of their fellow migrants deemed illegal job-seekers by the nation. The rally is the biggest ever held by migrants in the state.

More than 30,000 demonstrators marched peacefully in Tel Aviv,” police spokeswoman Lubra Samri told AFP.

The protesters gathered in the capital’s centre Rabin Square, chanting slogans like: “We are all refugees” and “yes to freedom, no to prison!” A three-day strike was also launched in several Israeli cities.

Continue reading…

Human Body Parts ‘fall from the sky’ in Saudi Arabia

jeddah locatorResidents of Saudi Arabia’s Jeddah were shocked to see human body parts suddenly falling from the night sky. Police say they may be the remains of a man who stowed away in an airplane’s wheel bay.

A photo claiming to be of the body of the fallen human being appeared in Arabic media and social media.

Police are investigating the incident, but would not comment if the body parts are connected to a Saudi airplane that made an emergency landing early Sunday morning.

The plane, carrying 315 passengers from Iran’s city of Mashhad, was forced to make an emergency landing in Saudi Arabia’s Medina after the cockpit reported a malfunction in the rear wheel. Twenty-nine people were injured during the approach.

Cases have been documented in the past of people – in a desperate attempt to cross borders – climbing into the landing gear of a plane before takeoff. Few survive the freezing temperatures when the plane is in the air.

Source

__

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: