የነብዩ ሕዝቅኤል ተዓምር – ከ2ሺህ ዓመታት በፊት የታየው መንኮራኹር
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on August 11, 2013

ከክርስቶስ ልደት በፊት፡ በ582 ዓ.ም ከሰማይ የሆነ ነገር፤ የሆኑ ነገሮች ወደ ምድር መጡ። ብሉይ ኪዳን ላይ ነብዩ ሕዝቅኤል ጌታችን ወደ ምድር መምጣቱንና አመጣጡም ምን እንደሚመስል በሚደንቅ መልክ አስቀምጦልናል። ነብዩ ሕዝቅኤል የሳለልን የእግዚአብሔር መንኮራኩር ቅርጽ ዋንኛ የሆኑትን የኢትዮጵያ ተዋሕዶ ዓብያተክርስቲያናትን ሕንፃዎች ይመስላሉ። እግዚአብሔር በዚያ ዘመን አንድኛ ልጁን በምድራችን ላይ ለመውለድ ተገቢ ነው የሚለውን ዝግጅት ለማድረግ ስለፈቀደ ይሆን ለነብዩ ሕዝቅኤል የታየው?
በሠላሳኛው ዓመት በአራተኛው ወር ከወሩም በአምስተኛው ቀን በኮቦር ወንዝ በምርኮኞች መካከል ሳለሁ ሰማያት ተከፈቱ፥ የእግዚአብሔርንም ራእይ አየሁ። [ሕዝቅኤል 1፥1]
በራሳቸውም ላይ ካለው ጠፈር በላይ ድምፅ ተሰማ፤ ሲቆሙም ክንፎቻቸውን ዝቅ ያደርጉ ነበር። በራሳቸውም በላይ ካለው ጠፈር በላይ የሰንፔር ድንጋይ የሚመስል የዙፋን አምሳያ ነበረ፤ በዙፋኑም አምሳያ ላይ እንደ ሰው መልክ አምሳያ ነበረ። ከወገቡም አምሳያ ወደ ላይ የሚብለጨለጭ የወርቅ ምስያ አየሁ፤ ከወገቡም አምሳያ ወደ ታች እንደ እሳት ምስያ አየሁ፤ በዙሪያውም ፀዳል ነበረ። በዝናብ ቀን በደመና ውስጥ እንደ ቀስተ ደመና አምሳያ፥ እንዲሁ በዙሪያው ያለ ፀዳል አምሳያ ነበረ። የእግዚአብሔር ክብር ምሳሌ መልክ ይህ ነበረ። ባየሁም ጊዜ በግምባሬ ተደፋሁ፥ የሚናገርንም ድምፅ ሰማሁ።[ሕዝቅኤል 1፥25-28]
__
Like this:
Like Loading...
Related
This entry was posted on August 11, 2013 at 20:56 and is filed under Curiosity, Ethiopia, Faith.
Tagged: ነብዩ ሕዝቅኤል, Bible, Bible Prophecy, Ethiopian Orthodox Tewahedo Churches, Ezekiel, Prophets, The Bible. You can follow any responses to this entry through the RSS 2.0 feed.
You can leave a response, or trackback from your own site.
Leave a Reply