Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2013
    M T W T F S S
     12
    3456789
    10111213141516
    17181920212223
    24252627282930
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for June 22nd, 2013

በዓለ መንፈስ ቅዱስ / ጰራቅሊጦስ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 22, 2013

Paraclete22አጋጣሚ? የእንግሊዙ ቴሌግራፍ ስለ ደብረ ዳሞ ይህን አቀረብገለባገለባውሲኤን ኤንእንኳን ያልተለምዶው ስለ ገዳማቶቻችን የሚለው አለ። ይህን ጽሑፍ በማቀርብበት በዚህ ሰዓት፡ ምስሉ ላይ የገባችው እርግብበመስኮቴ ብቅ ብላ ቁልጭ ቁልጭ ትልብኝ ጀመር። ቀስ ብዬ ፎቶ ካነሳኋት በኋላ፡ ጥሬ ስንዴ ለማምጣት ወደ መዓድ ቤት ገባሁ። ከፊሉን ስንዴ ለንፍሮ፣ ከፊሉን ደግሞ ለርግቧ ወስጄ ጣል ጣል ማድረግ ስጀምር እርግቧ ተንስታ በረረች። የበረረችበት አቅጣጫ ወደ ደቡብ ምስራቅ (የኢትዮጵያ አቅጣጫ) እንዲሁም ከኔ አንድ ኪሎሜትር ያህል እርቃ ልክ በዚያው አቅጣጫ ወደምትገኘው የመንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያንነው። ነገ ተነስተህ ወደዚያ መሄድ አለብህበማለት እርግቧ ምልክት እየሰጠችኝ መሆኑ ታወቀኝ። ወገኖቼን ይወደ ቤተክርስቲያኗ አመራለሁ፡ ከተቀቀለውም ስንዴበአብ፣ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እንቀምሳለን ማልተ ነውስብሐት ለእግዚአብሔር!

በዓለ መንፈስ ቅዱስ / ጰራቅሊጦስ

ይህች ታላቅ ዕለት ከቅድስት ሥላሴ አንዱ አካል የሆነው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ለቅዱሳን ሐዋርያት፣ ለቅዱሳን አርድእትና ለቅዱሳት ሴቶች የተገለጠባት ዕለት ናት፡፡ እነዚህ ሁሉ በጸሎት ተግተው በሚጸልዩበት ወራት መንፈስ ቅዱስ በተከፋፈሉ የእሳት ልሳን አምሳል የወረደበት ቅዱስ ቀን ነው፡፡

አስቀድሞ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን ሐዋርያት ደብረ ዘይት በተባለ ታላቅ ተራራ ላይ ሳሉ እንዲህ ብሎ አስተምሯቸው ነበር “ኀይልን ከላይ ከአርያም እስክልክላችሁ ድረስ በኢየሩሳሌም በጸሎት ቆዩ፡፡”/ሉቃ 2436/ መቶ ሃያው ቤተሰብም በኢየሩሳሌም ሀገር በምትገኝ በቤተ መቅደስ በአንድነት ሆነው በጸሎት በመትጋት ቆዩ፡፡ ልጆችዬ መቶ ሃያው ቤተሰብ የሚባሉት 12ቱ ሐዋርያት፣ 72ቱ አርድእት/አገልጋዮች/ እና 36ቱ ቅዱሳን አንስት/ሴቶች/ ናቸው፡፡

ከዕርገት በኋላ በአሥረኛው ቀን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሐዋርያት ወዳሉበት፣ በጸሎትና በምሥጋና ወደ ሚተጉበት ሥፍራ በእሳት አምሳል /ምሳሌ/ ወርዶ በእያንዳንዳቸው ላይ ተቀመጠባቸው፡፡ ይሄንንም ሁኔታ ተከትሎ ምስጢር ተገለጠላቸው፣ ይፈሩ የነበሩት ሐዋርያትም ወንጌልን ለማስተማር ደፋሮች ሆኑ፣ በተለያየ ቋንቋዎች እንዲናገሩ እውቀት ተሰጣቸው፤ የእግዚአብሔርንም ጸጋ ተቀበሉ፡፡ ይህንን ታላቅ ኀይል እና ሰማያዊ ስጦታን የሰጣቸውን እግዚአብሔርን በታላቅ ዝማሬና እልልታ አመሰገኑት፡፡

በዓለ ሃምሳ የሚባለውን የአይሁድን በዓል ለማክበር ከተለያዩ ሀገራት የመጡ በጊዜው የነበሩ ቁጥራቸው በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የሐዋርያቱን ታላቅ የዝማሬና የእልልታ ድምፅ ሰሙ፡፡ ከመቶ ሃያው ቤተሰብ መካከል አንዱ የሆነው ቅዱስ ጴጥሮስ የተሰበሰቡት ሁሉም እንዲሰሙት ድምፁን ከፍ አድርጎ ቃለ እግዚአብሔርን እንዲህ ብሎ አስተማራቸው፡፡ “እናንተ የእስራኤል ሰዎች ሆይ እኛን የሰው ልጆችን ለማዳን እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ወደ ምድር መጥቶ ከክፉ ሥራ ተመለሱ፣ ኀጢአትን አታድርጉ፣ በቅድስና ኑሩ፣ ወደ እኔም ተመለሱ ቢላችሁ፤ እናንተ ግን ምንም በደል ሳይኖርበት ገረፋችሁት፣ አንገላታችሁት፣ በመስቀል ላይም ሰቀላችሁት፡፡ እርሱ ግን እግዚአብሔር ነውና ሞትን ድል አድርጎ ተነሣ፡፡ እርሱ ግን አሁንም ይቅር ባይ ነውና ከኀጢአታችሁ ተመለሱ ንስሐም ግቡ ፡፡” በማለት አስተማራቸው፡፡

የተሰበሰቡት ሰዎች ሁሉ ተገረሙ፡፡ ምክንያቱም ሐዋርያት በፊት የሚያውቁት አንድ ቋንቋ ብቻ ነበረ፡፡ በዚህ ሰዓት ግን ሰባ ሁለት ቋንቋን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ገልጦላቸው ለሁሉም በየቋንቋቸው አስተማሯቸው፡፡ ይህንንም ድንቅ ተአምር ከተመለከቱት ብዙዎች እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡ ወደ ሐዋርያትም ቀርበው “አባቶቻችን እናንተ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናችሁና ምከሩን፡፡ እንደ እናንተ የእግዚአብሔር ልጆች እንድንሆንና በቅድስና እንድንኖር ምን እናድርግ?”በማለት ጠየቁ፡ በዚያች ቀን ቁጥራቸው ሦስት ሺ ያህል ሰዎች በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት አምነው ክርስቲያን ለመሆን ቀረቡ፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስም እንዲህ አላቸው፡፡ “እነሆ ሁላችሁም ንስሐ ግቡ፡፡ በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት አምናችሁ ተጠመቁ፡፡” አላቸው በዚያው ዕለትም ሦስት ሺ ሰዎች ወደ ሐዋርያት በመቅረብ ኀጢአታቸውን ተናገሩ፤ ሐዋርያትም እግዚአብሔር ይፍታችሁ እያሉ ልጅነትን የሚያሰጣቸውን ጥምቀት አጠመቁዋቸው፡፡

ከዚያ ቀን ጀምሮም በየዓመቱ ይህችን ታላቅ የቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን የምትባለውን በዓለ ጰራቅሊጦስን ክርስቲያኖች በታላቅ ደስታና ምሥጋና እናከብራታለን፡፡ እናንተም ልጆችዬ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት በቤተ ክርስቲያን ተገኝታችሁ ቅዳሴ በማስቀደስ፣ መዝሙር በመዘመር እና በመጸለይ ይህችን ታላቅ በዓል ልታከብሯት ይገባል፡፡

የእግዚአብሔር አብ ጸጋ የእግዚአብሔር ወልድ ቸርነት የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አንድነት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን፡፡

ምንጭ

_

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

Maid to Suffer

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 22, 2013

Re-blogged from

She had arrived in Oman from a small town in a remote part of Ethiopia full of hope. Hope that she had secured a good job as a maid in a prosperous country and would be able to send money to her family back home. She believed this fortuitous break might herald some much-needed luck and that a brighter future now beckoned for her far away from the confines of her poverty-stricken African homeland.

Her lucky break was in fact being found still alive after being raped and violated by her sponsor and three of his friends and dumped like a piece of rubbish in the desert to die.

When some locals came across her, she was bleeding and barely conscious, having spentten days in the desert. Doctors said she only survived because of the unusual prolonged rainy conditions, another piece of luck.

Not having friends or family to turn to or any embassy to provide shelter, she was alone and helpless.

Without the kindness of strangers, she would have died. Even then, she was arrested and jailed for two months because her Omani sponsor had alerted police in the Interior that she was a ‘run-away’ or absconder.

Now imagine this all happening to you when you’re only 16 years old. Not a worldly-wise girl either, but a young, unsophisticated woman who has never left her small town.

Continue reading…

__

Posted in Ethiopia, Infos | Tagged: , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: