Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • January 2012
    M T W T F S S
     1
    2345678
    9101112131415
    16171819202122
    23242526272829
    3031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for January, 2012

ግብጽ፡ በ ፌስቡክ በኩል ወደ ሻርያ ባርነት

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 27, 2012

በዓለም ዓቀፍ ዜና ማሰራጫዎች ቆስቋሽነት ተነስቶ የነበረውና የ አረብ ጸደይወይም የአረብ አብዮትእየተባለ ዓመቱን ሙሉ ሲወራለት የቆየው የአረብ እንቅስቃሴ ማዕበል በእስላማውያን የርዕዮተዓለም ቱጃሮች ተጠለፈ።

... በጃንዋሪ 25 2011 ላይ በካይሮው ታሂር አደባባይ ላይ ድንኳናቸውን ተክለው ለቀድሞው ፕሬዚደንት፡ ለሁስኒ ሙባረክ ከስልጣን መውረድ ምክኒያት የነበሩትና ዲሞክራሲ” “ነፃነትና” “ፍትሕናፍቆናል በማለት የተቃውሞ ድምጻቸውን ሲያሰሙ የነበሩት ዓለማዊ ሊበራልየሆኑት ግብጻውያን የተመኙትን የራሳቸውን ዲሞክራሲአሁን ለማግኘት በቅተዋል።

በዚህ ዲሞክራሲያዊ ሂደት፡ በታሂር አደባባይ አንድም ቀን ወጥተው ድምጻቸወን ለማሰማት ያልፈለጉት፡ ሙስሊም ወንድማማቾች እና ሳላፊዎች፡ ከሙባረክ እስር ቤት በመውጣት 70% የሚሆነውን የፓርላማ መቀመጫ እንዲረከቡ ተደርገዋል።

የግብጽ ሠራዊት በድብቅም ሆነ በግልጽ ከነዚህ የእስላም እንቅስቃሴዎች ጋር በመተባበር አሁን ሥልጣኑን ለማስረከብ መዘጋጀቱ እንግዳ ነገር ሊሆንብን አይችልም፤ ገና ከመጀመሪያው ጀምሮ ግብጽ ወዴት እንደምታመራ የታወቀ ነበርና። ባንዳንድ ነገሮቹ ይህ ሁኔታ ኢትዮጵያ ውስጥ በ1974 .. አካባቢ የነበረውን ሁኔታ ትንሽ መሰል ይላል።

የግብጽ ወደፊት ምን ይመስላል?

ሙስሊም ወንድማማቾቹና ሳላፊዎቹ (ልዩነታቸው ታክቲካዊ/ስትራቴጂካዊ አካሄድን በሚመለከት ጉዳይ ብቻ ነው) ስልጣኑን ከተረከቡ በኋላ የሚፈልጉትን እስላማዊ የሻርያ ሕግ መመሪያቸው አድርገው በይፋ ያጸድቃሉ። ይህን ለመቃወም የምእራቡ ደጋፊ የሆኑት ዓለማውያን የተቃውሞ ድምጻቸውን ለማሰማት ይሞክራሉ፡ ነገር ግን ዲሞክራሲየብዙኅኑን ፍላጎት መከተል ስላለበት ምንም ማድረግ አይችሉም። በጣሊያንና በጀርመን በዲሞክራሲያዊ መንገድ ሥልጣን ላይ ወጥተው የነበሩት ፋሽስቶች እና ናዚዎች፡ ሙሶሊኒንና ሂትለርን የመሳሰሉትን አምባገነን መሪዎች አፍርተው በኋላ ለጭካኔና ለእልቂት መብቃታቸውን ከታሪክ እንማራለን። በኛም ዘመን፡ በኢራን እንዲሁም በጋዛ በሕዝቡ ፍላጎት ሥልጣኑን የያዙት ኃይሎች ሕዝባቸውን በጣም አስከፊ ለሆነ ሁኔታ ማጋለጣቸው የምናየው ነው።

85% የሚሆነው ግብጻዊ እስልምናን ይመርጣል፣ የግብጽ መተዳደሪያ የእስላም ሻርያ ሕግ እንዲሆን ይፈልጋል፣ የሚሰርቅ ሰው እጆቹ እንዲቆረጡበት ይመኛል፣ ሴቶች እና ክርስቲያኖች እንደሁለተኛ ዜጎች ሆነው እንዲኖሩ ያቅዳል። ይህንንም የግብጻውያንን የልብ ትርታ በደንብ የተረዱት የእስላም ፓርቲዎች ሴቶች እና ክርስቲያኖች ፕሬዚደንት መሆን እንደማይገባቸው፡ እንዲያውም ቁልፍ የሆኑ የሥልጣን ቦታዎችን መያዝ እንደሌለባቸው በመተዳደሪያዎቻቸው አስቀምጠዋል። አሁንም ቢሆን፡ ክርስቲያን ግብጻውያን፡ ፖሊስ መሆን፣ በውትድራን ማገልገል፣ የእስላም ትምህርት ተቋሞች ውስጥ ገብቶ መማር ወይም ማንኛውም የብሔራዊ የስፖርት ቡድን ውስጥ የመሳተፍ መብት የላቸውም። ይህን አሳፋሪ ሁኔታ የዓለም ማሕበረሰብ እንደማያውቅ ሆኖ ዝም ብሎታል፣ እግዚአብሔር ግን አይረሳውም።

እነዚህ የእስላም ፓርቲዎች አንዴ ስልጣን ላይ ከወጡ ተመሳሳይ ምርጫ ከአራት ወይም አምስት በኋላ ለማድረግ ዝግጁዎች አይሆኑም። ስለዚህ ይህ የሰሞኑ ምርጫ ለመጀመሪያና ለመጨረሻ ጊዜ ተካሄደ ማለት ነው። ምዕራብውያን የዜና ማሰራጫዎች ዓመቱን ሁሉ በጥሩ መንፈስ ሲለፍፉለት የነበረው ይህ የአረብ ጸደይ” “እስላማዊ አብዮትእንደሆነ ዓለም ሁሉ ይረዳል፣ ምዕራቡ ታይቶ የማይታወቅ ትኩረት ሲሰጠው የነበረውና እኔ ግብጻዊ በመሆኔ ገና አሁን ኮራሁ” “እኛ ግብጻውያን አስተዋዮች ነን፡ የተማርን ነን፡ ማርና ወተት በሚፈስባት አገራችን ነጻነትና ዲሞክራሲ በቅርቡ እናስፍናለን!” እያሉ ጉራቸውን ሲነዙ የነበሩት ግብጻውያን ሁሉ ለቅሶአቸውን የሚያሰሙበት ቀን በቅርቡ ይመጣል።

የአረቦችን ዲያብሎሳዊ ተልእኮ እስካሁን ያልተገነዘቡት/መገንዘብ ያልፈለጉት ሞኝ አውሮፓውያን ተበድለናል!” በማለት ከግብጽ፣ ከሊቢያ፣ ከቱኒዝያ በቅርቡም ከሞሮኮና አልጀሪያ የሚፈልሱትን ስደተኞች በአገሮቻቸው ተቀብለው ለማስተናገድ ይገደዳሉ፣ የዚህ ሁሉ እባባዊ እንቅስቃሴ መሪ ሰይጣን ነውና።

የዲሞክራሲያዊ ምርጫ ተካሄደ፡ የተመረጡት እስላማዊ ፓርቲዎች ግን ለነጻነት፣ ለእኩልነት እና ለፍትሕ የቆሙ ኃይሎች አይደሉም፤ ሃይማኖታችን እስላም፣ ሕገ መንግሥታችን ሻሪያ፣ መሪያችን ሙሀመድ ነውየሚል ነው መመሪያቸው። ስለዚህ ዲሞክራሲ ሙስሊሞች በብዛት በሚኖሩባቸው አገሮች ሊሠራ አይችልም።

ብዙ ኃብትና ንብረቶች ያሉት፣ እንዲሁም በአሜሪካ እርዳታ እስከ አፍንጫው ድረስ የታጠቀው የግብጽ ሠራዊት ስልጣን የሚመኝ ከሆነ፣ በመጀመሪያ የእስላም ኃይሎች ፓርላማውን አሁን ለመያዝ እንደበቁት ሁሉ ለወደፊቱም የፕሬዚደንቱን ቦታ ከመካከላቸው መርጠው እንዲይዙ ያደርጋል፤ ከዚያም፡ በእስላም ፓርቲዎች መስተዳደር ሥር ግብጽ በሁሉም መስክ ወደ ውድቀት ስለምታመራ፣ ሠራዊቱ ተቃውሞውን በማሰማት፡ “እነዚህ ፓሪዎች 80 ሚሊየን የሚሆኑትን ግብጻውያን ለማስተዳደር ብቃት የላቸውም በሚል ሰበብ የመንግሥት ግልበጣ ለማድረግ ያስብ ይሆናል። ስለዚህ እነዚህ እስላማዊ ፓርቲዎች በመጀመሪያ የሠራዊቱን ዋና ዋና መሪዎች የተለያዩ ምክኒያቶች እየፈለጉ ካጠገባቸው ያስወግዳሉ። በቱርክም የምናየው ይህን ነው። ጄነራሎቹን ከመነጠሩ በኋላ ለዛባየሚባሉት ሙስሊም ወንድማማቾች ትክክለኛውን ገጽታቸውን ያሳያሉ። ሻርያ በሥራ ላይ ይውላል፤ ምንጠራና እጅ ቆረጣ ይጧጧፋል፣ ልክ እንደ ኢራን ግብጽም የእስላም ሪፓብሊክ የሚል ስያሜ ይሰጣታል። ይህም ሁኔታ በግብጽ የምጣኔ ሃብት ቀውስ እንዲፈጠር ይገፋፋል። ሳውዲ አረቢያና ኢራን ዘይት ባይኖራቸው ኖሮ የእስልምናው ሥርዓት ገና ዱሮ በጠፋ ነበር። ግብጽ ግን የተፈጥሮ ኃብት የላትም፣ መተዳደሪያዋ ከአሜሪካ የሚገኘው የገንዘብ ስጦታ፣ ከአውሮፓውያን ቱሪዝም የሚገባው ገቢ በተለይ ደግሞ የአባይ ውሃና የኢትዮጵያ አፈር ነው።

አሁን ግብጻውያን ይህን መርጠዋል፣ ሴቶቹም ይህን ተመኝተዋል። የመረጡትንና የተመኙትን አግኝተው ከራሳቸውና ከአካባቢያቸው ጋር እንዴት እንደሚኖሩ ከውጭ ሆነን ለምንታዘብ ይህ ትልቅ ትምህርት ነው። ኢትዮጵያን በሚመለከት በተለይ በኮፕት ክርስቲያኖች ላይ በደል ይፈጸማልና፡ የአባይ ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ በዚህ አጋጣሚ እንደ እነ አፄ ዳዊት ዘመን ቁልፍ የሆነ ሚና መጫወት ትችላለች፡ መጫወትም ይኖርባታል፡ ይህ ጥሩ ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።

በዚህ የቀውጥ ጊዜዋ፡ አሜሪካ ጥሩ መሪ ካገኘች ድጎማዋን ልታቆም ትችላለች፣ የቱሪዝሙም መስክ ሙሉ በሙሉ ገደል ሊገባ ይችላል። ለዚህ ሁሉ ጥፋት ሰበብ ይፈለጋል፣ ሰበበኞቹም 15 ሚሊየን የሚሆኑት ኮፕት ክርስቲያኖች ይሆናሉ፣ በደልና ግድያ በኮፕቶች ላይ ይቀጥላል፣ ዓብያተ ክርስቲያናት ይቃጠላሉ፣ ብዙዎችም ለመሰደድ ይገደዳሉ። የክርስቲያኖችን በአርብ አገሮች መገኘት የማይፈልጉትና፣ 15 ሚሊየን ያህል ኮፕቶች እስካሁን በግብጽ መኖራቸውን እንደ ኃፍረት አድርገው ሲወስዱት የነበሩት የእስላም ማሕበረሰቦች፡ ግብጽ ቀስበቀስ ከክርስቲያኖች መጽዳት ስለበቃች ይደሰታሉ፣ ይህንም እንደ ትልቅ ድል አድርገው ይቆጥሩታል።

ግብጽ፡ ላገሪቱ ብልጽግና ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሲያበረክቱ የነበሩትን፡ ቀደም ሲል፡ አይሁዶችን አሁን ደግሞ ክርስቲያኖችን ካጠፋች በኋላ ሙሉ በሙሉ በእስልምናው መንፈስ ሥር ትወድቃለች። ሴቶች እንዲሸፋፈኑ ይታዘዛሉ፣ ሴቶች የወሊድ ፋብሪካ ብቻ እንዲሆኑና ልጆች ብቻ እንዲፈለፍሉ ይገደዳሉ፣ በግብጽ የሕዝብ ቁጥር ጣራ ላይ ይወጣል፣ መንግስቱ አገሪቷን በደንብ ማስተዳደር ያቅተዋል፤ ድህነት፣ ረሃብ የእርስ በርስ ጦርነት በአገሪቱ ይንሰራፋል፣ አክራሪዎች አጋጣሚውን በመጠቀም ሕዝቡ እንዲከፋ ያደርጋሉ፣ ጦርነት ከእስራኤል ጋር ይጀመራል፣ ብዙ ግብጻውያን ወደ አውሮፓ ለመሰደድ ይበቃሉ። በአውሮፓም ሰው የስደተኞች ነገር ያንገፈግፈዋል፣ በስደተኞች ላይ ያማርራል፤ በዚህም ምክኒያት ቀኝ እና ብሔራዊ የሆኑ እንቅስቃሴዎች ስልጣኑን አሁን ካሉት ሶሺያል ዲሞክራቶች እና አረንጓዴዎች መረከብ ይጀምራሉ። በአውሮፓ ብሔራዊ አምባገነንት በየአገሩ ይንሰራፋል። በምጣኔ ኃብት ያልታደሉት አውሮፓውያን ወራሪ ሠራዊቶቻቸውን ወደ አፍሪካ እንደገና መላክ ይጀምራሉ።

 

________________________________

 

Posted in Curiosity, Ethiopia | Leave a Comment »

ለሕይወትህ አምልጥ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 22, 2012

አንድ በጣም ብርቱ ውሻ ስላለው የሩጫ ብቃት እያነሳ በሌሎች ውሾች ላይ ጉራውን ይነዛባቸው ነበር። ከዕለታት አንድ ቀን ታዲያ አንዲት ጥንቸል ሊያድን ወሻው ሊይዛት ስላልቻለ አመለጠችው። ሌሎቹ ውሾችም እንዲህ እያሉ ትሳለቁበት፦ የሩጫ ኃይልህ ወዴት ደረሰ? እንዴት አንዲት ደካማ ጥንቸል በሩጫ ልትቀድምህና ልታመልጥህ ቻለች?”

ውሻው ለጥቂት ደቂቃዎች ዝም ብሎ ከቆየ በኋላ ጥንቸሏ የምትሮጠው ሕይወቷን ለማዳን እኔ የምሮጠው ግን እራቴን ለማግኘት መሆኑን አትርሱ!” አላቸው።

ጥንቸሏ ውሻውን ልትቀድመው የቻለችው ሕይወቷን ለማዳን ስለምትሮጥ ነበር። ይሁን እንጂ ውሻው ይሮጥ የነበረው ጥንቸሊቷን ለማደንና ለመብላት ነበር። ለሕይወታችን ስንሮጥ ጠላታችን እንዳይዘንና እንዳይበላን ስለምንሮጥ ለየት ያለ ችሎታ ነው የሚኖረን።

ኃጢአት ነፍሶቻችሁን የሚአጎድልና ዘላለማዊ ሕይወታችሁን የሚያጠፋ መሆኑን ከተረዳችሁ ማምለጥ ኃይልና ድፍረት ነው።

ውሻ፡

ው፡ ው፡ ው፡ ው፡ ው፡

እግዚአብሔር ይመስገን የላይኛው ጌታ

እኔን የፈጠረኝ እንዳልንገላታ።

ውሻ በመባሌ ጥቂት ቅር ይለኛል፡

ባለሟል መሆኔን ማን ያስብልኛል።

 

ከፍጥረቶች ሁሉ ውሻ ርኩስ መባሌ፡

አልታወቀ ይሆን ከልፍኝ ውስጥ መዋሌ?

ሌሊት እየጮሁኝ ሌባ ሳላስቀርብ፡

አድራለሁ እስከጧት ተቀጥሬ ለዘብ።

ቀንም በሰንሰለት ታስሬ በፍንጅ፡

ጠላት አላስደርስ ከጌታዬ ደጅ፡

ላደን የወጣ እንዲሁ ጌታዬ ይዞኝ፡

እንኳን ያሳየኝን ወፍ አያመልጠኝ።

 

እንዲህ ስላልኳችሁ ቅዱስ ነኝ አላልኩም፡

ቅዱስንም ነገር ለኔ ስጡ አልልም፡

ተወስኗልና ጥንቱን በመጽሐፍም።

 

ከበላሁ ከጠጣሁ ምንም ብሆን ውሻ፡

ውለታ መላሽ ነኝ ለጌታዬ ጋሻ፡

ከቶ አልደለለም በባዕድ ሰው ጉርሻ።

 

በውሻነቴ እንዲሁ ስሜን የጠላችሁ፡

ችሎ ማደር ይሁን ለናንት ይመቻችሁ።

 

ሲዋሹም እንደሆን ወይም ሲደልሉ፡

ሲተረት ሰምቼ ደስ ብሎኛል ቃሉ፡

ለሰው ልጅ ሲያበሉ ለውሻ ልጅ ያብሉ፡

እስከዚህ ድረስ ነው የኔ ሙያ ሁሉ፡

ጌታዬን መውደዴ ታውቋል ባለም ሙሉ።

 

ደግሞ ልንገራችሁ የሰማሁትን ጉድ፡

አያድርም ይላሉ ቅቤ በውሻ ሆድ።

 

ባያየው ነው እንጂ ሆዱን ባይመረምር፡

ቅቤ አቅልጥ ያልሆነ አይገኝ ከፍጡር።

 

___________________________

Posted in Ethiopia, Life | Leave a Comment »

Timkat 2012: An Ethiopian Orthodox Celebration Of The Epiphany

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 19, 2012


The Feast of Timkat is the most important Christian holiday in Ethiopia. Timkat (baptism in Amharic), is the Ethiopian Orthodox celebration of the Epiphany. It celebrates the baptism of Jesus in the Jordan River by John the Baptist.

 

Continue reading…

Orthodox Christians celebrate the feast of Epiphany by jumping into freezing water

 

MELKAM TIMKET!

 ________________________________

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , | 1 Comment »

የረር ጽርሃ ሥላሴ ተዓምርና ምስጢር

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 16, 2012


 

 

ሰሞኑን ወደ የረር በር ሥላሴ ገዳም ጎራ ብየ ነበር። እንደሚታወቀው ይህ ገዳም የተሰራው ከ6 ዓመታት በፊት፤ ሁለት ግለሰቦች የተለያዩ ራዕዮች ከታዩአቸው ጊዜ በኋላ ነበር።

የመጀመሪያውን ራዕይ ያዩት አንዲት ሴትዮ ነበሩ። እኚህ ክርስቲያን ኢትዮጵያዊት አሁን ገዳሙ የሚገኝበትን ቦታ በወቅቱ በመግዛት አነስተኛ የሆነ ቤት ሠርተው መኖር ጀመሩ። ነገር ግን ይህን ቦታ ለቀው እንዲሄዱ የሚጠቁም ራዕይ በተደጋጋሚ ይታያቸው ነበር። ሴትዮዋም ይህን ራዕይ ቸል በማለታቸውና ኑሮአቸውንም እዚያው ቦታ ላይ ለመግፋት በመወሰናቸው እያበዱ መጡ። በዚህም ምክኒያት ከዓመት በኋላ ግቢውን ለቅው ለመውጣት ተገደዱ።

ቀጥሎም ራዕይ ለማየት የበቁት ግለሰብ አሁን ገዳም የሚገኝበት አካባቢ ላይ መሬት ገዝተው ከባለቤታቸው ጋር የሚኖሩት ሙስሊም ኢትዮጵያዊ፡ አቶ ቃሲም ናቸው። በራዕይ ተገለጠለት፡ ይመልከቱ

አካባቢው፡ በጣም ልዩ የሆነ፡ ባለታሪክ እና የተቀደሰ እንደሆነ ለእኝህ ሰው በራዕይ ይታያቸው ነበር። እዚህ ቦታ ላይ መሬት ሥር ተደብቆ የሚገኝ አንድ የጥንት ቤተክርስቲያን ሕንፃ እንዳለ እመቤታችን ድንግል ማርያም ለኚህ ግለሰብ በራዕይ ደጋግማ ትገልጽላቸዋለች።

ራዕያቸውንም ለሚያውቋቸውና ለሚመለከታቸው ወገኖች ሁሉ ለማጫወት ከበቁ በኋላ መጨረሻ ላይ ቤተ ክርስቲያኗ አለችበት ወደተባለው ቦታ ሁሉም አምርተው ቁፏሮ ይጀምራሉ። ግለሰቡ በራዕይ የታዩዋቸው ነገሮች ሁሉ መሬት ውስጥ ተቀብረው ይገኛሉ፡ ከነዚህም ውስጥ ጥንታዊ አጽሞች፡ መስቀላት እና ቅርሳቅርሶች ይገኙበታል።

4ኛው ምዕተ ዓመት ላይ በኢትዮጵያና አካባቢዋ ነግሥው ሲያስተዳድሩ የነበሩት አብርሃወአጽበሃ በሥላሴ ስም ይህችን ቤተከርስቲያን አሰርተዋት እንደነበር አሁን በደንብ ለማወቅ ተችሏል። ባካባቢው ገና ብዙ ምስጢራዊ የሆኑ ነገሮች እንደሚገኙ ይታመናል። ሣርና ዛፎች በሚገኙበት ቦታ ላይ ከየት እንደሚመጣ የማይታወቀው የሚጤስ ዕጣን ሽታ አልፎ አልፎ እንደሚሸታቸው ሰዎች ይናገራሉ። በጣም ቅዱስ የሆነ ጽላትም አሁን ቤተክርስቲያን የተሰራበት ቦታ አካባቢ ጥልቅ መሬት ውስጥ ተደብቆ እንደሚገኝ ነገር ግን እሱን እስካሁን ለማውጣት እንዳልተቻለ የኃይማኖት መሪዎች አውስተውኛል።

አሁን ቤተክርስቲያኗ በነበርችበት ቦታ ላይ የረር ጽርሃ ሥላሴ ገዳምበቆንጆ መልክ ተሰርቷል።

ቀደም ሲል የጠቀስኳት ሴትዮ መጀመሪያ ትኖርበት በነበረው ቦታ ላይ አንድ አነስተኛ ቤተመቅደስ ተሠርታለች።

ሴትዮዋም ሥላሴ ገዳም አጠገብ አንድ ቤት ተሠርቶላት ከልጅዋ ጋር እየኖረች እንዳልች ባለፈው መስከረም 2004፡ ልክ በሥላሴ ዕለት ፡ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታናለች። (እግዚአብሔር አምልክ ቀበላት!)

አቶ ቃሲም ከገዳሙ አጠገብ ከቤተሰባቸው ጋር አንድ አነስተኛ ሱቅ ከፍተው ይኖራሉ። አቶ ቃሲም ከቤተክርስቲያን ሰዎች ጋር በየጊዜው ይገናኛሉ፡ ነገር ግን ተባብሮ ለመስራት ፈቃደኛ እንዳልሆኑ እሳቸው እና ያነጋገርኳቸው የቤ/ክርስቲያን አገልጋዮች አውስተውኛል።

በቤተክርስቲያን በኩል አቶ ቃሲምን ለማስጠመቅ የተሞከረው ሙከራ ሁሉ ከሽፏል። አቶ ቃሲም ለመጠምቅ እና ክርስትናን ለመቀበል ፈቃደኛ አይደሉምና። እንዲያውም፡ እሳቸው፡ በድፍረት የቤተክርስቲያን አገልጋዮችን እንደሚሳደቡ፡ “ቄሶቹ የገንዘብ አፍቃሪዎች ናቸውእያሉ ስማቸውን እንደሚያጠፉ ነው የተነገረኝ።

አቶ ቃሲም፡ እኔ አሁን ለመጠመቅ ዝግጁ አይደለሁም!” “አባቶች በሚባሉትታሪክ አምናለሁ፡ ነገር ግን እኔን ለማጥመቅ ብቃት ያላቸው ቄሶች የሉም፡ ሁሉም የገንዘብ አፍቃሪዎች ናቸው…. በነገራችን ላይ ሙስሊም ራዕይ አይታየውምእየተባለ አይደለም አዲስ አበባ በየመንገዱ የሚወራው!?” እያሉ በማፌዝ አጫወቱኝ ነበር።

ይህም ሁኔታ በጣም ስላሳዘነኝ ነገሮችን ጠለቅ ብዬ ለመመርመር ሞከርኩ፤ ሁሉም የተወሳሰበ ስለሆነ ጉዳዩ ብዙዎቻችን ልናስብ እንደምንችለው ሆኖ መቀመጥ እንደማይኖርበት አሁን ተረዳሁ።

ይህ ቦታ ብዙ ታላላቅ ምስጢሮች የተደበቁበት እና መንፈሳዊ የሆኑ ጉዳዮች የሚገኙበት ቦታ ስለሆነ ከፍተኛ መንፈሳዊ ትግል ይካሄድበታል። ሰይጣን ከቅዱሳን ቦታዎች አይርቅምና ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ተንኮልን እየፈጠረ ቅዱስ መንፈስን (ሥላሴን) ለመፈታተን ይሞክራል።

አቶ ቃሲም ከጥሩ የኢትዮጵያ ክርስቲያን ቤተሰብ የወጡ፡ አባት እና እናታቸው ታማኝ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች እንደነበሩ፡ ባለቤታቸውም ክርስቲያን የሰሜን ሴት እንደሆኑ ተነግሮኛል።

50 ዓመት ዕድሜ የሚሆናቸው አቶ ቃሲም በወጣትነት እድሜአቸው ወደ አረብ አገር ሄደውና ሰልመው ከተመለሱ በኋላ ነበር ለዚህ የራዕይ ጸጋ ለመታደል የበቁት። የአባቶቻቸውን እና የእናቶቻቸውን እምነት የከዱት አቶ ቃሲም እስልምናን በመቀበል የኢትዮጵያን አምላክ ጨምረው ነበር የከዱት፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ቻይ፡ መሐሪ እና ሩህሩህ ነውና ለአባቶቻቸው፡ ለእናቶቻቸውና ለባለቤታቸው ሲል አንድ ሌላ እድል ሰጣቸው። እሱም፡ ፈጣሪአችን የኢትዮጵያ አምላክ እና ሥላሴ መሆኑን በእመቤታችን አማካይነት ገለጸላቸው፡ የተገለጸላቸውም ሁሉ ከነማስረጃው ፊታቸው ላይ ቀረበ፡ አቶ ቃሲም ግን ጥመቅትን የመሰለ ታላቅ ስጦታ ለመቀበል ወይም ለመጠመቅ ፈቃደኛ አይደሉም። እንዲያውም ሳዑዲ ዓረቢያ ሄጄ ሸሆችን ማማከር አለብኝ እያሉ በማቅማማት ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደ አምላኩ ታጋሽ፡ መሐሪ እና ሩህሩህ ስለሆነ፡ ተጠምቀህ ብትድን ጥሩ ነው፡ መዳን ትፈልጋለህን?” ብሎ ከመጠየቅ ሌላ ማንንም አስገድዶ ወደ እግዚአብሔር ኃይማኖት የመቀየር ፍላጎቱም የለውም። አቶ ቃሲም ያው ሥላሴ ቤተክርስቲያን አጠገብ ቤት ሠርተው ይኖራሉ። እዚያም ሆነው የቤተክርስቲያን አገልጋዮችን መሳደብና መገለማመጥ ችለዋል፡ ሆኖም ክርስቲያኑ ተገርሞ ራሱን ከመነቅነቅ በቀር ማንም ትንፍሽ ብሎ ሊነካቸው የቃጣ የለም።

ክርስቲያኖች እስላም በሆኑ አገሮች የሚደርሱባቸውን በደሎች ዓለም ሁሉ የሚያውቀው ነው። አረብ አገር የሚገኝ አንድ ክርስቲያን፡ እንኳን ሸሆችን እና ኢማሞችን እንዲህ በግልጽ ሊሳደብ እና መስጊድ አጠገብ ቤት ሰርቶ ሊኖር፡ መጽሐፍ ቅዱስን ይዞ፡ መስቀል አንጠልጥሎ ወደ አገራቸው ከገባ እንኳ ለእስራት፡ ለስቃይና ለግድያ ይበቃል።

ከዕለታት አንድ ቀን በግብጽ አገር ያሉ አንድ ሙስሊም ሸህ ፡ ታዋቂ የነበረውን ግብጻዊ ክርስቲያን መሀንዲስ መስጊድ እንዲሰራላቸው ይጠይቁታል። እርሱም በደስታ ፈቃደኝነቱን ይገልጽ እና መስጊዱን በደንብ አሳምሮ ይሰራላቸዋል። በዚህም ሥራው በጣም የተደሰቱት ሸህ ወደ መሀንዲሱ ዘወር ይሉና አሁን እስልምናን ተቀበል!” ብለው ይጠይቁታል፤ መሀንዲሱ ግን አይ አይሆንም እልምናን አልቀበለዐም በማለቱ አስገደሉት።

ክርስቶስ አምላክ፤ ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ሳያዩየሚያምኑ ብፁዓን ናቸውብሎ አስተምሮናል። ስለዚህ አሁን አቶ ቃሲም ታላቅ ፈተና ላይ ነው የሚገኙትክርስቶስን ወይም ሥላሴን የሚቀበሉት ቄሶቹን ወይም ሌላውን ለማስደሰት ብለው መሆን የለበትም፡ እግዚአብሔርን እንጂ። መዳን መፈለግ አለመፈለግ የራሳቸው መብት ነው፤ ግን ለጠፉት ሙስሊም ወገኖቻቸው አርአያ በመሆን ወደ ክርስቶስ መንግሥት እንዲመጡ ቀጥተኛውን መንገድ መምረጥ ነበረባቸው። በስድስት ዓመታት ውስጥ ስንት ሙስሊም መዳን በቻለ ነበር! የቤተክርስቲያን አገልጋዮች ጥፋት ወይም ድክመት የለባቸውም ማለት አይደልም፡ ሁላችንም ድክመት አለብን፡ ኃጢአተኞችም ነን፡ ነገር ግን እንኳን ከውጭ ሆነው ለሚታዘቡት አቶ ቃሲም ቀርቶ ክርስቲያኖችም እንኳ ቢንሆን በቤተክርስቲያን አገልጋዮች ላይ ምንም ዓይነት ስድብና ዘለፋ እንዲሁም ተቃውሟዊ ኃይለ ቃል የመሠንዘር መብት ሊኖረን አይገባም። የስድብና ፌዝ መንፈስ ከእግዚአብሔር አይደለምና!

አንድ ሌላ የታዘብኩት አሳዛኝና በጣም አደገኛ የሆነ ነገር የሚከተለው ነው፤

የሥላሴ ገዳምን አድራሻ ፈልጌ ለማግኘት በሞከርኩበት ወቅት የረር ሠፈር አንዳንድ ሰዎችን እጠይቅ ነበር። በአንድ ወቅት እስላማዊ አለባበስ የነበራቸው አንዲት ሲትዮ ወደኔ ጠጋ ብለው መጡና፡ “ “ቃሲም ሥላሴን” ነው እየፈልግክ ያለኽው? በዚህ በኩል ስትሄድ ታገኘዋለህ” ብለውኝ አለፉ። “ቃሲም ሥላሴ?” ፤ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? ብዬ እጅግ በጣም ተቆጣሁ። ወደ 20 የሚጠጉ የአካባቢውን ነዋሪዎችና ጎብኝዎች፤ “የዚህ ቦታ ስም መጠሪያ ምን ይባላል?” ብዬ መጠያየቅ ጀመርኩ። “ሥላሴ” “የረር ሥላሴ” “ሠፈራ ሥላሴ” ተብሎ እንደሚጠራ ነው በብዛት የተነገረኝ። “ቃሲም ሥላሴ” በማለት አንዳንዴ ለመጥራት እንደሚሞከርም ግለሰቦቹ በሃዘንና በንዴት ገልጸውልኛል። በርግጥም ገዳሙን በዚህ ዓይነት መልክ ለመጥራት መሞከሩ በጣም መጥፎ ብቻ ሳይሆን እጅግ ኃይለኛ መቅሰፍት አምጪም ነው።

ከዚህ በተረፈ ሦስት ዓብያተክርስቲያናት በነዋሪው ብርታት በሥላሴ ዙሪያ፡ ትንሽ ራቅ ራቅ ብለው ተሠርተዋል። ብዛት ያላቸው ሙስሊሞችም በቤ/ክርስቲያን አገልጋዮች ጥረት በየረር ጽርሃ ሥላሴ ተገኝተው በመጠመቀ እየዳኑና ክርስቶስንም እየተቀበሉ እንደሆነ ለማወቅ ችያለሁ።

ሥላሴ የተመሰገኑ ይሁኑ!

__________________________

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

ያለ ምላስ ከተፈጠረው ልጅ ሆድ 24 እባቦች ወጡ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 16, 2012


አካለ ስንኩል (ሽባ) ሆኖና፡ እጅ እና እግሩ በአካሉ ተሣሥረውበት የነበረው የቄሱ ልጅ በሥላሴ ጠበል ከሽባነት እየተላቀቀና እየተፈወሰ ነው። ምላስ እንኳ አፉ ላይ ሳይወጣለት የተፈጠረው ይህ ልጅ በውስጡ አስረውት የነበሩት 24 እባቦች በጠበል ተነቅለው ከሆዱ ከወጡለት በኋላ፡ እጆቹና እግሮቹ ተዘረጉለት፡ ምላሱ ወጣለት፡ የባሕር አንበሳ እንደሚያሰማው ዓይነት ድምጽ ቢተነፍስም አሁን ቀስበቀስ መናገርም ጀምሯል።


___________________________

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

በእውነተኛና ሃይማኖት ባለው፡ በቆራጥ ሕዝብ ዘንድ፡ መልካሙ ኹሉ ይቻላል!

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 15, 2012

 

ኢትዮጵያ ሆይ፥ ሀገራችን! ረስቼስ እንደኾነ፡ ቀኜ ትርሳኝ፣

ያላሰብሁሽ እንደኾን፡ መላሴ ትናጋዬን ሰልቶ ይውጋኝ።

አቤቱ ፈጣሪያችን፡ በኢትዮጵያ ቀን፡ ጠላቶቿን ኹሉ አስብ፤

አፍርሷት፡ ኢትዮጵያን፡ እስከመሰረቷ ድረስ፡ የሚሉትንም ሕዝብ።

እናንት ትምክህተኞች፡ የኢትዮጵያ ጸሮች፥ የተነኰላችሁን ብድራት፤

የሚመልስ ነው አምላካችን፡ በፍትሕ በተአምራት፤

በሚጠሉሽ ላይ፡ በእውነት፥

በቅን ለሚፈርደው ንጉሥ፡ ምስጋናችን ይብዛለት።

ኢትዮጵያ ሆይ፥ ሀገራችን! ረስቸሽ እንደኾነ ቀኜ ትርሳኝ።

 

ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት“(የተደበቁ የኢትዮጵያ ምስጢሮች)ከሚለው የንቡረ እድ ኤርምያስ ከበደ ወልደ ኢየሱስ ሦስተኛ መጽሐፍ የተወሰደ።

ከታላቅ አክብሮትና ምስጋና ጋር።

ዛሬ ባሉትም ሰዎች ዘንድ፡ እንደጥንቱ እየተፈጸመ ከመቀጠል በቀር፡ ሌላ ዕድል ሊኖረው አይችልም! ምክኒያቱም እውነታ፡ እርግጥ በበለጠ እየጨመረና እየተጠናከረ የኼደ መኾኑን፡ ይኸው፡ እየረሳችን ምስክር በመኾን፡ በገሃድና በግዘፍ እናየዋለን፡ ይኹን እንጂ፡ እየራሳችን ምስክር በመኾን፡ በገሃድና በግዘፍ እናየዋለን፡ ይኹን እንጂ፡ ከሰነፎችና በሰነፎች የሚቀርበው፡ እንዲህ ያለው ምክንያት፡ እዚያው፡ ለሰነፎች የሚያገለግል፡ የሰነፎች፡ ከንቱና ፍሬቢስ አሳብ ሰለሆነ፡ በእኛ፡ በቀዱሱ ኪዳን ኢትዮጵያውያን ዘንድ፡ ፈጽሞ ቦታ የለውም።

በሓሰተኞችና በእምነተቢሶች ዘንድ፡ ክፉው ኹሉ እንደሚቻል፡ እንዲሁ፡ በእውነተኛና ሃይማኖት ባለው፡ በቆራጥ ሕዝብ ዘንድ፡ መልካሙ ኹሉ ይቻላል! አንድ ቆራጥ ሕዝብ ከፈለገ ኹሉን ማድረግ የሚቻለው መኾኑን ለማመልከት ባመኑበት እምነታቸውና በፈለጉት ሥርዓታቸው ማንነታቸውን አኩርተው፥ መሪዎቻቸውንም አቅፈው፡ የኃያላን ተቃዋሚዎቻቸውን ጥቃት ተቋቁመው፥ በውጭ ተፅዕኖም ሳይበገሩ፡ ይህን እውነታ፡ በግብር ያረጋገጡ ሕዝቦችን በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል።

ከእነዚህም መካከል የዛሬውን ትውልዷን አያድርግባትና ከቀደሙት ታማኞቹ ኢትዮጵያውያን ልጆቿ፡ ምግባርና ገድል የተነሣ፡ ቀንደኛ ኾና በመልካም ምሳሌነት የምትጠቀሰው፡ ኢትዮጵያ መኾኗ፡ በባለጋራዎቿ ዘንድ ሳይቀር የተመሰከረ እውነታ ነው። ለዚህ ቆራጥነት ስለሚያበቃው፡ ሃይማኖታዊ ሥነ ምግባር፡ በዓለም ላይ የሚኖሩት ሕዝቦች፡ የተለያየ ግምት፡ እንዳላቸው፡ ከዚህ የሚከተለው፡ የጊዜያችን ኹነት በቀላሉ ሊያስረዳ ይችላል፦

ከጥቂት ዓመታት በፊት፡ በመካከለኛው ምሥራቅ፡ ኢራቅ ኩዌይትን በወረረች ጊዜ፡ አሜሪካውያንና ምዕራባውያን አገሮች፡ በነዳጅ በኩል ያላቸውን ጥቅም ለመጠበቅ ሲሉ የቃል ኪዳን ጦር አደራጅተው ኩዌይትን በመርዳት ጎረቤቲቱን ሳዑዲ ዓረቢያን ጭምር፡ ከወረራው ማትረፋቸው ይታወሳል። ይህን በመሰለው እርዳታቸው፡ ሊዋጉላቸው፡ ወደእነዚሁ የእስልምና አገሮች የኼዱትን፡ አሜሪካንና የጦር ጓደኞቿን፡ ሳዑዲ ዓረቢያ፡ በቅድሚያ ካስገባቻቸው ግዴታዎች መካከል አንደኛውን ልጥቀስላችሁ! እርሱም ለእርዳታ የደረሱላት ክርስቲያኖቹ ምዕራባውያን የጦር ጓደኞቿ፡ በሳዑዲ ዓረቢያ ምድር ላይ፡ ሃይማኖታውያን የኾኑ፡ የጸሎትም ኾነ የሰንደቅ ዓላማ፥ ወይም የበዓል ሥርዓቶቻቸውን፡ በምንም መንገድ እንዳይፈጽሙ የሚከለክለው ነበር።

ይህም ማለት፡ እናንተ ክርስቲያኖች፡ የክርስትና ሥርዓታችሁን፡ በእስልምና ምድራችን ላይ ከምትፈጽሙ ይልቅ፡ እስላሙ ጠላታችን ኢራቅ ወርራን፡ አገራችንን ብትይዝ ይሻለናል!” በማለት፡ ቅድሚያውን ለሃይማኖቻቸው መስጠታቸው ነው። በተቃራኒው ደግሞ አሜሪካና ምዕራባውያን ተባባሪዎቿ፡ እናንተን ሳንረዳ፡ ሃይማኖታችንን ከምናስከብር ይልቅ፡ ለገንዘብ ጥቅማችን ስንል ሃይማኖታችን ቀርቶ እናንተን ብንረዳ ይሻለናል!”ማለታቸው ነው።

ምሥራቃውያንና ምዕራባውያን፡ ስለሃይማኖት ያላቸው አስተሳሰብና ግምት እንግዴህ በዚህ ተለይቶ ይታወቃል። ኢትዮጵያ፡ ከእግዚአብሔር ያገኘችው፥ ጥንታዊ፥ ቀዳሚና የራስዋ የኾነ ሕዝባዊ የአስተዳደር አቋም የሌላት ይመስል፥ እነርሱም ዛሬ እየሠሩበት ያለው ከዚሁ ከእርሷ የወረሱት መኾኑን ለማዘናጋት በመሞከር በአሜሪካና በቀሩት ምዕራባውያን አገሮች ግፊት፡ በኢትዮጵያ የሕዝባዊ አገዛዝ ሥርዓት (democracy/ዲሞክራሲ) መስፈን አለበት!” ተብሎ ለዚህ ትውልድ ይህን ያህል ነጋሪት የሚደለቅለት ለምን እንደኾነ በቀላሉ መመልከት ነው።

የሳዑዲ ዓረቢያ ሕዝብ፡ ከአሜሪካውያንና በጠቅላላ ከምዕራባውያን ጋር ያለው ግንኙነት ያው በገንዘብ ላይ የተመሠረተ ኾኖ፡ የቱን ያህል የጸናና የተንሰራፋ እንደኾነ በይፋ ይታወቃል። ይኹን እንጂ ግንኙነቱ እንዲህ እጅግ የተቀራረበና የተጠናከረ እንደመኾኑ፥ አገሩም በፈረንጆቹ የሥልጣኔ ምርት እንደመጥለቅለቁ መጠን ሕዝቡ በሃይማኖቱ ላይ የተመሠረተውን ሥነ ምግባሩን ቋንቋውንና ፊደሉን፥ አለባበሱንና ሌላውን ባህሉን በይበልጥ አጠናከረ እንጂ በምንም መንገድ አልለወጠም።

እንዲያውም ዐረቦች፡ የዘመኑን ትውልዳቸውን በእስላማዊው ሃይማኖታቸው ሥርዓተ ትምህርት እያነፁ በማሳደግ እያዘጋጁት ያሉት በክርስቲያኖቹ ምዕራባውያን ላይ በጠላትነት እንዲነሣ መኾኑ በይፋ የሚታወቅ ከመኾኑ ጋር፡ በአሁኑ ጊዜ፡ ከምዕራቡ የክርስቲያን አህጉር ላይ በእስልምና አክራሪዎች ታውጆ እየተካኼደ ያለው ዓለም አቀፍ የ”ሽብር” ጦርነት በቂ ማስረጃ ነው።

ኢትዮጵያም እኮ እስከዚህ እስከዛሬው ትውልድ ድረስ እንደዚህ ነበረች። ያውም በ፯ሺሆች ዓመታት ለሚቆጠር ዘመን። ዛሬ ግን ይህ ትውልድ ከላይ የተጠቀሱትን የአባቶቹንና የእናቶቹን ምሳሌያዊ ምክር ባለማጤንና ባለማስተዋል ወይም ቸል በማለት ወይም በመናቅ እንኳንስ ዓበይት የኾኑትን የተከበሩ ውርሶቹን ሊንከባክብ ይቅርና፡ ጥቃቅንና ተራ የኾኑትን እንኳ መጠበቅ አቅቶት ይኸው፡ ጨርሶ ለመውደቅ፡ ሲፍገመገም ይታያል።

የኢትዮጵያውያን አንዱ የጨዋነታቸው መገለጫ የኾነው የመከባበር ባህላችን በዚህ ትውልድ እየተዳከመ በመኼድ ላይ ይገኛል፤ ለምሳሌ አንድ ኢትዮጵያዊ ቀደም አድርጎ የማያውቀውንና በዕድሜው ከእርሱ ላቅ ያለ መስሎ የሚታየውን ማንንም ሰው፥ ወንድ ኾነ ሴት፡ “እርስዎ” በማለት ወደ “አንቱታ” ደረጃ ከፍ ያደርገዋል፥ ወይም ያደርጋታል እንጂ፡ እንዲያው ተነሥቶ ወንዱን “አንተ!” ወይም ሴቷን፡ “አንቺ!” አይልም ነበር። ዛሬስ፡ ይህ ባህል፡ በምን ኹኔታ ላይ ይገኛል ይህስ የመከባበሩ ባህላችን እየቀረ መኼዱን አያመለክትምን?

የሥጋ ወላጆችን፥ ወንድሞችንና እኀቶችን ብቻ ሳይኾን፡ አዛውንቶችን ወንዶች፡ “አባባ” ወይም ታላላቆችን፡ “ጋሼ” ፥ አዛውንቶችን ሴቶች ደግሞ “እማማ” ወይም ታላላቆችን “እትዬ” ብሎ የመጥራቱ መልካም ባህላችን ደብዘው ሳይቀር፡ እየጠፋ መኼዱን ይኸው እየተመለከትን ነው። እንዲያውም በዚህ ፋንታ በባዕዳን ቋንቋ፡ Father! Mother! Brother! Sister! እያሉ መጥራት በኅብረተሰቡ ዘንድ ሙሉ ተቀባይነትን አግኝቶ ተጠሪዎቹም፡ በደስታ፡ ወንዶቹ “ወይ!” ወይም “አቤት!”፥ ሴቶቹ፡ “ወይ!” ወይም “እመት!” እያሉ ፈጥነው መልስ በመስጠት ተባባሪነታቸውን ሲያረጋግጡ ይታያል። በነገራችን ላይ “አቤት!” የሚለው ምላሽ የሚሰጠው፡ ጠሪው ወንድ ሲኾን ብቻ እንጂ ለሴት ጠሪ ፈጽሞ “አቤት!” አይባልም፤ ነውር ነው። ለሴት ጠሪ፡ ተጠሪው ምላሹን መስጠት ያለበት “እመት!”ብሎ ነው።

ለዚህም፡ ለኹለተኛው ቁም ነገር፥ በቂ ምክንያት አለ፤ ይኸውም “አቤት!” “አብ የት?” ማለት ሲኾን፡ በግእዝ፡ “አቡየ” አባቴ፥ “አይቴ” የት ማለት ስለኾነ፡ “አባቴ! የጠራኸኝ፡ ወደየት (ወዴት)ልትልከኝ ነው?” ፥ እንደዚሁ ኽሉ “እመት!” “እም የት? ማለት ሲኾን በግእዝ “እምየ” እናቴ፥ “አይቴ”፡ የት ማለት ስለኾነ “እናቴ! የጠራሽኝ፡ ወደየት (ወዴት)ልትልኪኝ ነው?” ማለት ነው ተብሎ ይተረጎማል።

የአለባበሳችን ባህል ስለሚገኝበት ሁኔታ ስንነጋገር በጣም የሚያሳዝነን ነገር ይኖራል። ይኸውም ይህ የዛሬው የኢትዮጵያ ትውልድ በአለባበሱ ረገድ የራሱን ባህል ጨርሶ ትቶ፡ ፈጽሞ አውሮጳዊ፥ ወይም ምዕራባዊ ወይም ፈረንጅ በመኾኑ ነው።

ዘመናዊውን ትምህርት ከተማረው፥ ከጥራዝ ነጠቁና ከከተሜው መካከል በአኹኑ ጊዜ የአገራችንን ልብስ ለዓውደ ዓመት እንኳ የሚለብሰው ስንቱ ነው? እጅግ ጥቂቶች ናቸ፤ ምናልባት የመልበስ ፍላጎት ኖሮአቸው የሚለብሱ ቢኖሩ እንኳ እነርሱ አለባበሱን ስለማያውቁበት አንድ ባዕድ የኾነ ሰው፡ “እንዲህ አድርገህ ልበሰው!” እየተባለ እንደሚናገረው ተዋናይ መስለው እንደሚለብሱት የሚታወቅ ነው።

በአሁኑ ጊዜ ከጥንታውያኑ የዓለም አህጉር መካከል በዘመኑ ትውልዷ ምክንያት በአጠቃላይ ኹለንተናዋ “ባለቤቱ፡ በቤቱ ባይተዋር፡ ባይተዋሩ በሰው ቤት ባለቤት” የኾነባት አገር ቢኖር ኢትዮጵያ ኾና ትገኛለች። ይህ ዝቅጠት አያሳዝንምን? አያሳፍርምንስ?

የዘመኑን ዓለማዊ ሥልጣኔ እንደሃይማኖት በተከተለው ወገን ዘንድ ከአገር ልብሱ ብቻ ሳይኾን ከለባሹም ሰው ይልቅ የክብሩን ቦታ የያዘው የባዕዳኑ ልብስ ስለኾነ የኢትዮጵያዊነት አንዱ ምልክት የኾነውን “ነጠላ” ወይም “ኩታ” ደርቦ መታየት ለዚያ ሰው በዘመናዊ ትውልድ ዘንድ የመጨረሻውን የውርደትና የንቀት ምልክት ተጎናጽፎ እንደመታየት የሚያስቆጥር ከመኾን ደረጃ ተደርሷል። ይህን እውነታም፡ “ባለኩታ”፥ ወይም “ኩታ ለባሽ” የኾነው ኢትዮጵያዊ የዚህ መጽሓፍ አዘጋጅ በራሱ አገር፥ በራሱ ወገኖች ሳይቀር ሲናቅና ሲዋረድ አይቷል። አዎ! በነገራችን ላይ “በራሱ አገር በራሱ ወገኖች”አያስብልም ምክኒያቱም በባዕዳኑ ዘንድማ እየተደነቀና እየተከበረ ነው ያለው። የተናቀውና የተዋረደው እኮ በራሱ አገር፥ በራሱ ወገኖች ዘንድ ብቻ ነው።

ይህ ኹኔታ የደረሰው በኩታውና በባለኩታው አገር በኢትዮጵያ ከዚያም ይባስ፡ በአገሩ በኢትዮጵያ ስም በሚጠራው አየር መንገድ ነው። ባለኩታው ኢትዮጵያዊ ወደባሕር ማዶ የሚበርበትን የጉዞ ወረቀቱን (Ticket)ለማስቆረጥ፡ በመናገሻዪቱ ከተማ ውስጥ ካሉት የአየር መንገድ ጽሕፈት ቤቶች መካከል በአንዱ እንደተገኘ በተራው የተቀበለችው ጸሓፊ ባለጉዳዩ ባልጠበቀው መልክ አነጋግራና የጉዞ ወረቀቱን አዘጋጅታ እስከሰጠችው ጊዜ ድረስ ለአንድም አፍታ ቀና ብላ ዓይን ለዓይን ሳታየው ከእርሱ ለቀረበላት የምስጋና ሰላምታም እንኳ አጸፋውን በአግባቡ ሳትመልስለት አሰናበተችው።

 

Continue reading in PDF>EthioBahel

 

_______________________________________

 

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

Exposed: The Military’s Freakiest ‘Non-Lethal’ Weapon Ideas

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 10, 2012

Tasers that elicit excruciating spasms in one person at a time? Foam pellets that send an entire crowd fleeing in agony? Pfft. So 2011. Where non-lethal weapons are concerned, the future’s all about sonic microwaves that can make swimmers puke mid-stroke, and aircraft with laser beams that can redirect an entire enemy plane mid-flight.

Or, at least, those are the deepest, darkest wishes of the Pentagon agency responsible for non-lethal weapons.

The military’s Joint Non-Lethal Weapons Directorate’s “Non-Lethal Weapons Reference Book,” leaked online last week by PublicIntelligence.org, is a terrifying treasure trove that describes dozens of ways — some already in-use, others in development or still mere fantasy — for military and law enforcement officials to make you wish they were using the real bullets.

A total of 14 weapons, according to the reference book, are currently being fielded. Some of ‘em, you’ve heard of. Good old tasers, which the guide helpfully reminds us “can penetrate 2 inches of clothing” in order to “totally disable an individual,” and guns that shoot 600 rubber pellets filled with pepper spray to keep rowdy crowds — already used by law enforcement officials, sometimes with very lethal results — subdued.

Continue reading…

Plus

US non-lethal weapon ‘wish list’ revealed on the net

Are We Prepared?

Have you ever made an electromagnetic weapon? To make one, what you need is simply a microwave oven. The magnetron in the oven, a simple electronic circuit and a small foldable antenna, would give the device a radiation level strong enough to up-set a number of electronic systems used in banking, security, military, medical and public service control operations. A more powerful weapon can be developed with a slightly expensive magnetron available in most of the super markets in former Soviet Union countries. This weapon, which can be mounted in a car, could generate enough power to destroy many electronics and also make control systems run mad, even when operated at a long distance. The USA and other NATO alliances have developed much more powerful weapons that can cause mass destruction without a single ‘bang’.


There are a number of ways a terrorist may use these electromagnetic weaponry to attack military and civil targets. A landing aircraft would typically be at a height of 100m at 2 km distance from the edge of the runway. For an example, in the case of an airport, with an adjacent road, free vehicular movement maybe well within this distance. An electromagnetic emitter fixed to the roof of an automobile can direct a strong dose of radiation towards the plane as it passes by, causing the internal electronic network to fibrillate resulting the collapse of the aircraft. The consequences maybe even severe if the intruder strike the control tower of the airport by electromagnetic means.


In the present context, an even graver scenario is the illumination of vulnerable positions at ground level with electromagnetic waves by a low flying light enemy air-craft. Such an air-craft may carry a sizable radiator and kill many electronics without arousing much alarm in the neighbourhood.


In 1967, the USS Forrestal was involved in one of the worst cases of electromagnetic interference ever documented. During a carrier landing, a military aircraft was exposed to the ship’s radar (electromagnetic radiation) and accidentally fired its munitions hitting a fully armed and fuelled aircraft on the deck. The explosions caused severe damage to the carrier and resulted in 134 deaths. These incidents were unintentional but the question is ‘why a similar incident cannot be carried out intentionally?’


When antilock braking systems (ABS) were first introduced, problems arose in Germany on the autobahn when brakes were self-applied as the autos passed a nearby radio transmitter. Not only the braking system but the engines and many other options of the modern automobiles are fully computer controlled, and vulnerable to electromagnetic attacks. A group of Swedish scientists conducted a test few years ago on how external electromagnetic sources can interfere with the automation system of vehicles. This group has reported that the engine of a Volvo Car in motion can be subjected to a dead standstill within a fraction of a second by directing an electromagnetic pulse emitted from a microwave generator installed a few hundreds metres away by the road side. Such a sudden stoppage in a highway may cause a terrible pileup of which the outcome is beyond imagination.


The medical care industry has also been affected by EMI. A heart attack victim in US died when the attached monitor and defibrillator shut down every time the radio transmitter was used in an ambulance.


At very close distance apparently harmless devices such as mobile phones, portable computers and radios may act as lethal electromagnetic emitters. These electronic devices emit a low power signal while they are in use. They may induce small voltages in the conductors in the close vicinity, which will traverse into critical systems. For an example when you use a cellular phone inside a plane the signals emitted by the transmitter of the phone may generate voltage pulses in the communication wires hidden inside the wall panel adjacent to the seat. These pulses may propagate into the electronics of the control panel.

Continue reading…

_________________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia | Tagged: , , , , , , , | 5 Comments »

Merry Christmas / Genna Ethiopia

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 6, 2012

 

የምሥራች

 

የምሥራች ደስ ይበለን

የዓለም መድኃኒት ተወለደልን

የምሥራች ደስ ይበለን

ጌታችን ተወልዶ አይተነው መጣን

ንጉሥ ሄሮድስ ይህን ሲሰማ

ፈልጋችሁ አምጡት በቀን በጨለማ

አሽከሮቹም እንደታዘዙት

በኮከብ ተመርተው ሕፃኑን አገኙት

ሰገዱለት ከመሬት ወድቀው

ወርቅና ዕጣኑን በረከቱን ሰጥተው

 

The Ethiopian Christmas known as Ganna is celebrated on January 7th. This celebration takes place in ancient churches carved from solid volcanic rock and also in modern churches that are designed in three concentric circles. Men and boys sit separately from girls and women. Also the choir sings from the outside circle. People receive candles as they enter the church. After lighting the candles everyone walks around the church three times, then stands throughout the mass, which may last up to three hours. Food served at Christmas usually includes injera, a sourdough pancake like bread. Injera serves as both plate and fork. Doro wat, a spicy chicken stew might be the main meal. A piece of the injera is used to scoop up the wat. Baskets decorated beautifully are used to serve the wat. Gift giving is a very small part of Christmas celebration. Children usually receive very simple presents such as clothing. In Ethiopia Christmas day is January 7, so on Christmas Eve the city is crowded with pilgrims from all parts of the country. They remain outdoors all night, praying and chanting. In the morning, a colorful procession makes its way to a nearby hilltop where a service is held. Three young men march at the head of the crowd, lashing whips from left to right to keep the people in line. Those who worship are fed with bread and wine that has been blessed by priests. After the service is over the rest of the day is spent dancing, playing sport and feasting.

 

FROM SANTA’S NET

 

__________________________________________

 

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: