Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • October 2011
    M T W T F S S
     12
    3456789
    10111213141516
    17181920212223
    24252627282930
    31  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for October 10th, 2011

ይሉኝታ፡ የዜና ማሰራጫዎች በሽታ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 10, 2011

የወቅቱን የዓለማችንን ሁኔታ በቅርብ ለሚታዘብና አገራቱንም በደንብ ተዘዋውሮ ለመመልከት አጋጣሚው ያለው ሁሉ የመጀመሪያዋና የመጨረሻዋ የክርስትና ምድር ምናልባት ኢትዮጵያ አገራችን ብቻ ልትሆን እንደምትችል ለመመስከር ይችላል።

ምንም እንኳን ትውልዳችን ሞኛሞኝ፥ ደካማና ለጠላት በቀላሉ ተጋልጦ የሚኖር ትውልድ ሆኖ ቢታየንም፡ ጽኑ በሆነ የክርስቲያናዊ ሕይወት ጎዳና ተግቶ የሚጓዘው ኢትዮጵያዊ ቁጥር ከምንገምተው በላይ በጣም ከፍ ያለ ነው። በአሁኑ ጊዜ በተለይ ኢትዮጵያውያን ወጣት ሴቶች፡ እናቶችና ልጆች ናቸው የክርስትናችንና የኢትዮጵያውነታችን ጽኑ መከታዎች ሆነው የሚገኙት። ጠላቶቻችን አንዳንድ መንፈሰደካማ የሆኑ ሴቶቻችንን እንደምሳሌ በመውሰድ የወገኖቻችንን ስም ለማጥፋት ይጥራሉ፡ እኛም በቀላሉ የምንሰማውና የምናየው ይህ ብቻ ስለሚሆን እህቶቻችን ሁሉ የተበላሹ እንደሆኑ አድርገን ለመውሰድ እንበቃለን። ይህ ግን እጅግ በጣም የተሳሳታና ከእውነትም የራቀ ነገር ነው። ሴቶቻችን ከምንግዜውም በበለጠ ጥልቅ መንፍሳዊ ጉዞ ላይ ይገኛሉ፥ ሴቶቻችን አስደናቂ በሆነና ትጋት በተሞላበት መልክ የዓብያተ ክርስቲያናቱን ግቢዎች ዕለት ተዕለት እየሞሉ ጸሎታቸውን ያደርሳሉ። ይህ ሁኔታ እስካሁን አለመታየቱና ተገቢውን ትኩረት አለማግኘቱ በጣም ሊያሳዝነን ይገባል።

ባጠቃላይ ግን፡ የኢትዮጵያ ወጣት በሚያገኘው አጋጣሚ ሁላ የክርስትና ሕይወቱን በሚገባ ለመኖር ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። መንፈሳዊ ጦርነት ላይ እንገኛለንና፡ ክርስቲያኑ በየትምህርት ቤቱ፡ በየገባያው፡ በታክሲና በየአውቶቡሱ የቅዱሳንን ምስሎች በመለጠፍና መስቀልንም በማንጠልጠል ለጠላቶቹ ድምጽአልባ የሆነ ኃይለኛ መልእክት በማስተላለፍ ላይ ይገኛል። ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ፥ ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው” (መዝ.59:4)

ታዲያ ይህ በእንዲህ እንዳለ፡ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ የብዙኃን ዜና ማሰራጫዎች ደግመው ደጋግመው የሕዝቡን ኃይለኛ የልብ ትርታ ለማዳመጥ አሻፈረኝ ይላሉ፥ ክርስቲያኖችንና ክርስትናን፡ ማለትም፡ ኢትዮጵያውያንን በቸልታ ማለፉን ይመርጣሉ። የሬዲዮና የቴሌቪዥን ጣቢያዎች፤ እንዲሁም ጋዜጦችና መጽሔቶች ሁሉ በክርስትና ላይ ለማመጽ በአንድነት ውል የገቡ ይመስላሉ፡ ከእሁድ እስከ እሁድ ያለማቋረጥ የሚያወሩት፡ የሚያሳዩትና የሚጽፉት ስለ ፖለቲካ፥ ስለ ገንዘብ፥ ስለ ዘፈንና ዳንኪራ ብሎም ስለ እንግሊዝ እግርኳስ ጨዋታ ብቻ ነው።

የክርስትና እምነታቸው በተሸረሸረባቸው የምዕራቡ ኢዱስትሪ አገሮች እንኳ ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች በየሰንበቱ የጸሎት ስነሥርዓት ከዓብያተ ክርስቲያናት በቀጥታ ያስተላልፋሉ። የክርስቲያኖች ደሴት በሆነችው ኢትዮጵያ ግን ቴሌቪዥኑ በቅዱስ ሰንበት ፈጣሪን በትንሹም ቢሆን በማስታወስ ፈንታ፡ እንደ ኢትዮጵያን አይደልወይም ፖሊስና እርምጃውየመሳሰሉት ፕሮግራሞች ደጋግሞ ማቅረቡን ይመርጣል። ጸረክርስትና፡ ጸረክርስቲያን እየሆኑ በመጡት የአሜሪካ እና አውሮፓ አገሮች የዜና ማሰራጫዎች እንደ ፋሲካእና ገናለመሳሰሉት በዓላት የሚሰጡት አትኩሮት አሁንም አልቀነሰም፤ ሪዲዮና ቴሌቪዥን ጣቢያዎች በዓላቱ ከመድረሳቸው ከሣምንታት በፊት ነው የገና ዜማዎችን የሚያሰሙት፥ ምርጥ የገና ዜማ ሰሌዳዎችንም ያወጣሉ፤ የሮማው ፓፓስ ሆኑ ነገሥታቱና የአገር መሪዎቹ ሁሉ ለሕዝቦቻቸው የሚያቀርቡትን መልዕክት በሬዲዮና ቴሌቪዥን በቀጥታ ያስተላልፋሉ። ቀንደኛ ኢአማንያን እንደሆኑ የሚታወቁት እንደ Bill Mahr የመሳሰሉት ታዋቂ አሜሪካውያን የቴሌቪዥን ሰዎች ሳይቀሩ አሁንስ በዛ! ከቤተሰብ ጋር አብረን የምናከብረውን የገና በዓላችንንማ አንነጠቅምበማለት እየመጣ ወዳለው አስከፊ ጊዜ ይጠቋቁማሉ።

ታዲያ በpolitical correctness (ይሉኝታ)በሽታ የተለከፈው   የምዕራቡ ዓለም እንኳ ማንነቱን ገና ሙሉ በሙሉ ለመካድ ሳይነሳሳ፡ ለምንድን ነው የኛዎቹ መሪዎች፡ ጋዜጠኞችና ጣቢያዎቻቸው አባቶቻቸው ለታገሉለትና ለሞቱለት የክርስትና ሕይወት ግድየለሽነትን የሚያሳዩት? በትዕግስተኛውና በዝምተኛው ሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታን እያሳደረ የመጣውን ይህን ሁኔታ አይተው አስፈላጊውን የማሻሻያ እርምጃ ለመውሰድስ እስካሁን ለምን ተሳናቸው?

_____________________________________________________

Posted in Ethiopia, Media & Journalism | Tagged: , , , | Leave a Comment »

On The Fall of Man

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 10, 2011


St. John Maximovitch

The world was created good and called to the joy of life in union with the Source and Creator of life, the Lord God.

The first to sin and to be torn from this union were angels. The angelic realm was split: some remained with God; others, in their pride, desired to live their own life, independent of God. The angelic world was split and sin was born there, but the earthly world remained good.

And then the devil, which means “the one cast down from heaven,” began to strive to join the earthly realm to himself. The highest creation on earth, man, had been given a commandment by God not to eat of the tree of knowledge of good and evil. Why was the commandment given? This tree was just like all the others, and in itself it had no outstanding characteristics. No, the knowledge of good and evil was not in the tree itself, and not for this reason was the commandment given. The Lord gave it because man was created free, and the Lord desires of man a freely-willed striving and longing for union with God. The commandment was given because only through its fulfillment could man express his freely-willed striving toward God and love for Him. And blessedness consists simply of communication with God through love of Him.

The devil is burdened by his separation; he is perpetually in a state of wrath and vengeance, and it comforts him to attract others. The devil never appears as his true self, but takes on various appearances. Then in paradise he took on the appearance of a serpent, and gave man the idea that the commandment had not been given for the expression of man’s love of God, but so that man would not become like God. The devil planted the thought that the command was issued, not out of God’s love, so that man would dwell in God’s love, but because God desires to dominate, and to prevent man from being as God, and coming to know the endless and limitless joy of being.

When man came to believe this diabolical idea, he was instantly separated from God. Everything changed, and man could no longer enjoy life in God and speak with God freely and straightforwardly as children speak. There was no peace, no joy, and man began to hide from God. Everything changed, the link between God and man was destroyed and nature ceased to heed man. Weeping entered the world, and the soul became burdened.

______________________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: