Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • October 2011
    M T W T F S S
     12
    3456789
    10111213141516
    17181920212223
    24252627282930
    31  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for October, 2011

አረብ በመሀረብ አርብ፡ “የመጨረሻ ተስፋየ የአገሬ ፀበል ብቻ ነው”

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 26, 2011

ታች ላይ የሚገኘውን ፊልም በቅርብ የቀረጸው የፌደራል ጀርመን ብሔራዊ የቴሌቭዥን ጣቢያ ነበር። ፊልሙ ላይ ከቀረቡት ዋና ዋና ቁምነገሮች መካከል የሚገኙትን መልእክቶች እናገኛለን፦

  • 600.000  የቤት አገልጋዮች በትንንሾቹ የተባበሩት የአረብ ኢሚራቶች ይኖራሉ።

  • 80%  የሚሆነው የኢሚራቶች ነዋሪ ስደተኛ ሠራተኛ ነው።

  • ኢትዮጵያውያን ሴቶችን ወደ አረብ አገር የሚልኩት የአዲስ አበባ ወኪሎች የሚገኙት በመርካቶ ገባያ አካባቢ ነው። ብዙዎቹ ወኪሎች ፈቃድ የላቸውም። ለምሳሌ፣ ፋይዛ የጉዞ ወኪል

  • አብዛኛዎቹ ወደ አረብ አገር የሚሄዱ ክርስቲያን ኢትዮጵያውያን ሴቶች ስማቸውንና ሃይማኖታቸውን እንዲቀይሩ ይደረጋሉ።

  • እንደ ትርንጎያሉት ኢትዮጵያውያን የቤት ሠራተኞች ዱባይ ሲገቡ ገና በአውሮፕላን ማረፊያው ነው ፓስፖርታቸውና ተንቀሳቃሽ ስልካቸው በአስቀጣሪዎቹና በቀጣሪዎቹ የሚነጠቀው።

  • ኢትዮጵያውያን የቤት አገልጋዮች በየቀኑ እስከ 20 ሰዓት፡ ሳምንቱን ሙሉ እንዲሰሩ ይገደዳሉ፡ ምግብም በቀን አንዴ ብቻ ያገኛሉ።

  • የወር ደምወዛቸው ከ120 ዩሮ አይበልጥም፡ እሱም አንዳንዴ ጭራሽ አይከፈላቸውም።

  • ከጨካኝ አሰሪዎቻቸው በደል ያመለጡ 400 የሚሆኑ ሴቶች በዱባይ እስር ቤቶች ውስጥ ይማቅቃሉ። ለመብታቸው የሚከራከርላቸው ማንም የለም። እንዲያውም የእስር ቤት ጠባቂ ፖሊሶች ሴቶቹን በየጊዜው ይደፍሯቸዋል።

  • ዱባይ ውስጥ ተቃውሞን ወይም ብሶትን መግለጽ አይፈቀድም፥ ለመስማትም ሆነ ለመርዳት ዝግጁ የሆነ መንግሥታዊ ወይም መንግሥታዊ ያልሆነ ዓለም ዓቀፍ ድርጅት የለም።

  • የቤት ሠራተኞችን ኢሰብዓዊ የሆነ አኗኗር ለመከታተል ዱባይ የሚገቡ ጋዜጠኞች ክትትል ይደረግባቸዋል፡ ይህ የጀርመን ቴሌቪዥን በድብቅ የቀረጻቸው ፊልሞች በዱባይ ባለስልጣናት እንዲደመሰስ ተደርጓል። (የፖሊስ አገር!)

  • በኢትዮጵያ ሙስሊሞች የሚተዳደረው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ትርንጎን ለመሳሰሉት የኢትዮጵያ ተወላጆች ግልጋሎት አይሰጥም፡ እሷን በሚመለከት ከእዚህ የቴሌቪዥን ቡድን ጋርም ለመተባበር ፈቃደኛ አልነበረም፡ እንዲያውም ኢትዮጵያውያንን በመርዳት ፈንታ እነርሱን ለዱባይ ባለሥልጣናት አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ሪፖርቱ ያመለክታል።

  • ኢትዮጵያውያኑን ለመርዳት ፈቃደኛ ሆኖ የተገኘው በዱባይ የኢትዮጵያ ኢምባሲ ሳይሆን፡ አጠገቡ የሚገኘው የፊሊጲንስ ኢምባሲ ነው። (ሐዋርያው ፊሊፖስ የኛ አምባሳደር ተንከባካቢ ስለነበር ይሆን?)

  • በፊሊጲንስ አገር የቤት ሠራተኞች ተጨማሪ የቤተሰብ አባል እንደሆኑ ተደርገው ነው የሚቆጠሩት ፡ በዱባይ ግንባሪያየሚል ስም እየተሰጣቸው ይገረፋሉ፡በፈላ ውሃ ይቃጠላሉ።

ትዕቢተኛዋ ባቢሎን ሰማይ ጠቀስ ፎቆችን መስራት ትወዳለች፤ ብልጭልጭ በሆኑ ነገሮች ታሸበርቃልች፤ በጥቁር ወርቅም ሰክራለች፤ ለቅንጦትና ምድራዊ ለሆነ ምቾትም እንቅልፍ አጥታ ትኖራልች፡ ሰውን የመሰለ ክቡር ፍጡርን ግን ትንቃለች፣ ታንቋሽሻለች።

ትርንጎ የት እንደደረሰች ለማወቅ የቴሌቪዥን ቡድኑ አልቻለም። ግን የትም ትድረስ የትም፡ እነዚህ አረማዊ የአረብ ማህበረሰቦች በዚህች ምድር ላይ የተሰጣቸውን የቤት ስራ እየሰሩ አይደሉም፡ ምናልባትም የመጨረሻውን ፈተና በኢትዮጵያውያኑ አማካይነት ለመውደቅ እየበቁ ነው ፤ እንዲያውም የመጥፊያ ጊዚያቸው መቃረቡን በአገሮቻቸው እየተቀጣጠለ ያለው እሳት ፈጋ አድርጐ እያሳየን ነው።

በጣም የሚያሳዝነው፡ በእነ አባ ጂፋር ጊዜ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያትን በባርነት ሲሸጡ የነበሩት ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች አሁንም በተመሳሳይ መልክ ይህን አጸያፊ ድርጊት በመፈጸሙ ረገድ ክፍተኛ ሚና ለመጫወት መብቃታቸው ነው። እስላም በሆኑ አገሮች ኢትዮጵያን እየወከሉ የሚሄዱት ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ናቸው። እነዚህ ኢትዮጵያ አገራችንና ኢትዮጵያውያትን ያገለግሉ ዘንድ ዱባይን በመሳሰሉ የአረብ ከተሞች በየቪላው የተቀመጡት ዲፕሎማቶች የሚሰቃዩ ወገኖቻቸውንለመርዳት ፈቃደኞች አይደሉም።

90ዎቹ ዓመታት የአዲስ አበባ ከንቲባ እንዲሆን ተሹሞ የነበረው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ስልጣኑን ያለአግባብ በመጠቀም ባጭር ጊዜ ውስጥ በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የመስጊድ ግንባታ ጂሃዳዊ ዘመቻ በኢትዮጵያ ዋና ከተማ አካሄደ። ከዚህ ድርጊት በኋላ ይህ ግለሰብ ምንም ዓይነት መንግሥታዊ ኃላፊነት ሊወስድ አይገባውም ነበር፡ ነገር ግን በሱዳኗ ካርቱም የኢትዮጵያአምባሳደር ሆኖ ለመሾም በቃ፡ ባለፈው መስከረም ላይም አንድ ታላቅ የኪነጥበብ በዓል እዚያው አዘጋጀ። ይህን መሰሉ ዝግጅት ነፃ በወጣችዋና በአዲሲቷ ሱዳን መቅረብ ሲገባው፡ በክርስቲያኖችና በዳርፉር ጥቁር እስላሞች ላይ ጭፍጨፋውን ስታካሂድ ለነበረችው፡ እንዲሁም የኢትዮጵያን መከፋፈል ለምትመኘዋ ለካርቱም ተሰጠ። ከዚያም ወደዚህ የኪነጥበብ ትዕይንት በዓል ሲያመሩ የነበሩ የትግራይ ኪነጥበብ ቡድን ዓባላት በመኪና አደጋ ሕይወታቸውን አጡ። ለመሆኑ ይህ በካርቱም የተቀመጠው አምባሳደር በጋበዛቸው ዘፋኞች ሕይወት መጥፋት ላይ ምን ዓይነት ሚና ተጫውቶ ይሆን?

ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?” [ማር. 836]

ስቃይ በዱባይ #1


ስቃይ በዱባይ #2

ስቃይ በዱባይ #3


ስቃይ በዱባይ #4

ስቃይ በዱባይ #5


__________________________________________

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ሀይሌ ገብረሥላሴ፡ የኖበል ሽልማት እንዳገኘሁ አድርጌ እቆጥርዋለሁ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 21, 2011

ጀግናው ኢትዮጵያዊ አትሌት፤ ሀይሌ ገብረሥላሴ እነ ራውል ጎንዛሌስን በመርታት የዚህ ዓመቱ ከፍተኛ የስፔይን አስቱሪያስ ልዑል ሽልማት ተቀበይ ለመሆን በቅቷል።

ነገ ዓርብ በአስቱሪያስ ዋና ከተማ በኦቪዬዶ በሚካሄደው የሽልማት ስነሥርዓት ላይ የሚገኘው ኃይሌ 50.000 ዩሮ እንዲሁም በዝነኛው የስፔይን ሰዓሊና ኃውልት ሠሪ በጆዓን ሚሮ የተነደፈ አንድ አነስተኛ ኃውልት ይረከባል።

እንኳን ደስ ያለን፥ ሀይሌ!

ተጨማሪ መረጃ

http://www.as.com/mas-deporte/articulo/gebre-premio-recibir-nobel/20111020dasdasmas_4/Tes

http://www.marca.com/2011/10/20/atletismo/1319112485.html?a=543b15a786699a919a4cdfc73c6833e1&t=1319160890

http://www.elmundo.es/multimedia/?media=clEkYlx07Sc

 

ሀይሌ በሽልማቱ ስነስርዓት ላይ

 

http://www.marca.com/2011/10/21/atletismo/1319226185.html

http://www.elpais.com/articulo/deportes/Gebrselassie/recibe/Premio/Principe/Asturias/elpepudep/20111021elpepudep_18/Tes

 

___________________________________

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

ሰይጣናዊ የአዲስ ዓለም ስርዓት ምልክቶች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 16, 2011

ዓለማችን በአጋንንት (ሰይጣን) ምልክቶች ተወራለች፡ እነዚህን ምልክቶች ፈለግንም አልፈለግንም በየቀኑ ሳናይ የምናልፍበት ሰዓት የለም። እነዚህን ምልክቶች ችላ ማለት ትልቅ ስህተት ብቻ ሳይሆን ሰይጣንን ለማገልገል ነፍሳቸውን ለሸጡት ተኩላዎችና ቀጣፊ ነጣቂዎች ወደ በረት እንዲገቡ በር መክፈትና እራስንም አሳልፎ መስጠት ነው።

በምንገኝበት ዘመናችን በግለሰቦች ላይ ተደጋግሞ የሚንጸባረቀው ሰይጣናዊ ምልክት ታች የምናየው ነው

ይህንንም ምልክት በተለይ፡ በባለሥልጣናት፣ በማናጀሮች፣ ለንዋይ በሚገዙ ወይም በገንዘብ አፍቃሪዎች ላይ፡ በሰዶማውያን – ባጠቃላይም በአጋንንት የተጠመዱ ግለሰቦች ላይ – ሲንጸባረቅ ለማየት እንችላለን።

Horned God Represents the horned god of witchcraft. Pan or Cernunnos. Note the thumb under the fingers and given by the right hand.

Horned Hand The sign of recognition between those in the Occult. When pointed at someone it is meant to place a curse. Note the thumb over the fingers and given by the left hand.

አጋንንት በመንፈሳቸው ሰው ላይ ሲያድሩ ዓይነተኛ መገለጫቸው ሰውነታዊ መንገላታትን ማሳየት ነውና፡ የእጅ እንቅስቃሴ ይህን ሁኔታ በግልጽ ይጠቁመናል። ስለዚህ፡ ለዚህ አደገኛ መንፈስ የተጋለጡት በጠበል፣ በጸሎት በቤተ ክርስቲያን ሥልጣን በእግዚአብሔር ስም ሊታሠሩና ኃይላቸው ሁሉ ሊነጠቅ ይገባዋል።

በጥንቆላው ዓለም ተወዳጅነት ካላቸው ምልክቶች አንዱ ባለ አምስት ማዕዘኑ ኮከብ (Pentagram) ነው። ይህም ምልክት መሬትን፡ ነፋስን፡ እሳትና ውሃን ባካባቢያቸው ከሚገኙት መናፍስት ጋር ያለውን ነገር ሁሉ የሚወክል ምልክት ነው። ይህን ምልክት በባንዲራዎቻቸው (ሰንደቅዓላማ)ላይ አስፍረው የሚገኙት ሁለት አገሮች ኢትዮጵያና ሞሮኮ ብቻ ናቸው።

ዋናዋናዎቹ ሰይጣናዊ የምስል ምልክቶች

Baphomet Unique to Satanism. A demonic deity and symbolic of Satan. Can be seen as jewelry. It is also now being used by the masons. It can be seen on their buildings and the emblems the put on their vehicles to identify each other.

Ankh Symbolizes fertility rites and the building up of lust within a person. A spirit of Lust is the power of this union of male /female representations. Also called the Long Life Seal.

Upside Down Cross Symbolizes mockery and rejection of Jesus. Necklaces are worn by many satanist’s. It can be seen on Rock singers and their album covers.

Satanic “S” Represents a lightning bolt that means “Destroyer”. In mythology, It was the weapon of Zeus. Worn to have power over others. Also was worn by the feared SS of Nazi Germany.

Cross of Nero – Or Peace sign. Another sign that mocks the cross of Jesus. Also know as “The Dead Man Rune”. It appears on the tombstones of some of Hitler’s SS troops.

Satanic Cross Upside down question mark that questions the Deity of God. Within the occult it is the representation of the three crown princes; Satan, Belial and leviathan. Symbolizes complete power under Lucifer.

All seeing Eye Believed to be the eye of Lucifer and those who claim control of it have control of world finances. Used in divination. Hexes, curses, psychic control and all corruption are worked through this emblem. This one is a symbol of the Illuminati. Look at U.S. currency. This one is the basis of the New World Order.

Seal of the Left Hand Path Indicates Black magic and the path to Satan.

Star and Crescent Represents the moon goddess Dianna and the “son of the morning”, the name of Lucifer in Isaiah 14:12. Witchcraft uses it the way shown and Satanism turns it in the opposite direction.

Blood Ritual Symbol Represents animal and human sacrifices.

Veve Designs used in Voodoo to summon the various Loa or spirit deities. Symbol for Baron Samadi, Lord of the graveyard and death.

Scarab Beetle The dung beetle which is the Egyptian symbol of reincarnation. It is also a symbol of of Beelzebub, Lord of the flies (satan). Worn by occultists to show that they have power and is a source of protection.

Anarchy Means to abolish all laws. In other words “do what thou wilt” the law of Satanists. Used by Punk rockers and Heavy Metal followers.

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | 3 Comments »

Anti-Christian Britain — A Disturbing Trend Emerging

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 12, 2011

Last month a Christian owner of a Café where bible verses were being displayed on television screens was told (quite incorrectly) by police that he was breaking the law.

The fact that British police would consider the displaying of Christian scripture an illegal offence is a concerning indication of the mentality that British society has come to adopt towards all things Christian.

For anyone who follows the British media’s reporting of American politics, the continuous attempt to run down certain American politicians on account of their faith rather than engaging with their politics has now become a rather boring familiarity.

Bush and Palin are crazed evangelical fundamentalists we are forever being told, oh yawn, is this kind of cheap and lazy defamation really what we have to make do with for journalism?

Yet what is far more concerning is what is happening to Christians here in our own country. It is only when one steps back and takes an overview of the litany of cases where Christians have been discriminated against for their religious convictions, that it is possible to appreciate what resembles a sustained assault against the Christian communities in Britain.

Whether it is the case of the nurse who was suspended for offering to pray for a patient, the van driver who faced disciplinary action if he refused to remove a palm cross from his dashboard, the couple who were prohibited from fostering because of their Christian beliefs or the supply teacher who was dismissed when she mentioned praying for a child’s family. The list goes on and on.

Then there are the truly bizarre cases of town councils choosing not to put up their annual display of Christmas decorations or the BBC dropping the use of the terms BC and AD because of their Christian connotations.

It is as if there is a systematic effort to extrapolate British society from its Christian heritage and the values that have for centuries served as a basis for British culture and identity. Those who have been responsible for these moves have often advocated for them on the grounds of creating a more secular and therefore a supposedly more inclusive and pluralistic society for everyone.

Yet it is hard to escape the fact that it has often been the very same people who have promoted secular values when it has come to driving out Christian aspects of public life, who have simultaneously lent their support for the establishment of a parallel religious legal system in the form of Sharia law courts.

Indeed there seems to be a curious disparity here.

How is it that the media has often lambasted Christian individuals who have found themselves dismissed from work or even in court on account of their views on sexuality and yet concurrent to this we hear so relatively little about those hard-line Islamic preachers who have openly preached hate over issues of gender and homosexuality, issues that the liberal press claims to champion.

At our universities these speakers are often provided with an open platform on the grounds of free speech and freedom of religious expression. Those were the kind of arguments that many in the British media were at pains to stress when discussing the ground zero mosque in Manhattan. And while our media obsessed over supporting the building of one mosque in America, it all but ignored the burning down of countless churches elsewhere in the world, not to mention the massacring of Coptic Christians in their Churches in Egypt or the murder of Iraqi Christians in their places of worship there.

Yet this is symptomatic of a growing double standard. We all remember the crowds who turned out for the protest at the Pope rally last year but where were the demonstrations against the then Mayor Ken Livingstone sponsoring the visit to London by the extremist cleric Yusuf al-Qaradawi?

The reality now seems to be that in Britain, Christians are treated by entirely different standards to that thought appropriate for other religious groups. It is as if Christians and their faith have become fair game. But it should not be left to Christians to campaign on this issue alone.

As much as I am not a Christian, it still seems clear that all of us who value the rights and freedoms afforded by a liberal democracy should ensure that there is fair treatment for Christians in Britain.

More than that, we as a society need to recognize that Christianity has played a major and for the most part extremely positive role, in forming our nation’s history and national identity.

Those who cannot bring themselves to understand this will naturally also prove unable to appreciate what it means to actually be British and our society will continue to suffer from the chronic loss of values and any sense of purpose that currently seems to be at the heart of so many of the social challenges that we now face.

Source: Huffingtonpost, posted: 11/10/11

BBC is anti-Christian and ageist, viewer survey finds

The BBC uses “derogatory stereotypes” to portray Christians while marginalising older women, according to the corporation’s own research.

Viewers and staff expressed concerns about “tokenism” and diversity “box-ticking” and warned that positive discrimination was skewing recruitment.

Many people believe the corporation retains a politically Left-wing or “liberal bias” and that religions other than Christianity were sometimes better represented, according to they survey.

The report based on the poll results, obtained by the Daily Mail, concluded: “In terms of religion, there were many who perceived the BBC to be anti-Christian and as such misrepresenting Christianity.”

It added: “Christians are specifically mentioned as being badly treated, with a suggestion that more minority religions are better represented despite Christianity being the most widely observed religion within Britain.”

One respondent was quoted as saying: “As a Christian I find that the BBC’s representation of Christianity is mainly inaccurate, portraying incorrect, often derogatory stereotypes.”

Another added: “Seldom do we find a Christian portrayed in drama, and when we do, it is usually a “weak” person or a “bigot”.”

The BBC generated blasphemy protests from Christian groups in 2005 when it aired Jerry Springer: The Opera, which became one of the most complained about shows in television history.

A BBC spokesman said: “We have strict editorial guidelines on impartiality, including religious perspectives, and Christian programming forms the majority and the cornerstone of our religion and ethical output.”

Source: The Telegraph

_____________________________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia | Tagged: , , , , , , , | 2 Comments »

Shocking Video From Egypt: US-funded Egyptian Military Murdering Christians

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 11, 2011

 

F.A.Q. on U.S. Aid to Egypt: Where Does the Money Go—And Who Decides How It’s Spent?

 

Continue reading…

 

_____________________________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , | Leave a Comment »

ይሉኝታ፡ የዜና ማሰራጫዎች በሽታ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 10, 2011

የወቅቱን የዓለማችንን ሁኔታ በቅርብ ለሚታዘብና አገራቱንም በደንብ ተዘዋውሮ ለመመልከት አጋጣሚው ያለው ሁሉ የመጀመሪያዋና የመጨረሻዋ የክርስትና ምድር ምናልባት ኢትዮጵያ አገራችን ብቻ ልትሆን እንደምትችል ለመመስከር ይችላል።

ምንም እንኳን ትውልዳችን ሞኛሞኝ፥ ደካማና ለጠላት በቀላሉ ተጋልጦ የሚኖር ትውልድ ሆኖ ቢታየንም፡ ጽኑ በሆነ የክርስቲያናዊ ሕይወት ጎዳና ተግቶ የሚጓዘው ኢትዮጵያዊ ቁጥር ከምንገምተው በላይ በጣም ከፍ ያለ ነው። በአሁኑ ጊዜ በተለይ ኢትዮጵያውያን ወጣት ሴቶች፡ እናቶችና ልጆች ናቸው የክርስትናችንና የኢትዮጵያውነታችን ጽኑ መከታዎች ሆነው የሚገኙት። ጠላቶቻችን አንዳንድ መንፈሰደካማ የሆኑ ሴቶቻችንን እንደምሳሌ በመውሰድ የወገኖቻችንን ስም ለማጥፋት ይጥራሉ፡ እኛም በቀላሉ የምንሰማውና የምናየው ይህ ብቻ ስለሚሆን እህቶቻችን ሁሉ የተበላሹ እንደሆኑ አድርገን ለመውሰድ እንበቃለን። ይህ ግን እጅግ በጣም የተሳሳታና ከእውነትም የራቀ ነገር ነው። ሴቶቻችን ከምንግዜውም በበለጠ ጥልቅ መንፍሳዊ ጉዞ ላይ ይገኛሉ፥ ሴቶቻችን አስደናቂ በሆነና ትጋት በተሞላበት መልክ የዓብያተ ክርስቲያናቱን ግቢዎች ዕለት ተዕለት እየሞሉ ጸሎታቸውን ያደርሳሉ። ይህ ሁኔታ እስካሁን አለመታየቱና ተገቢውን ትኩረት አለማግኘቱ በጣም ሊያሳዝነን ይገባል።

ባጠቃላይ ግን፡ የኢትዮጵያ ወጣት በሚያገኘው አጋጣሚ ሁላ የክርስትና ሕይወቱን በሚገባ ለመኖር ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። መንፈሳዊ ጦርነት ላይ እንገኛለንና፡ ክርስቲያኑ በየትምህርት ቤቱ፡ በየገባያው፡ በታክሲና በየአውቶቡሱ የቅዱሳንን ምስሎች በመለጠፍና መስቀልንም በማንጠልጠል ለጠላቶቹ ድምጽአልባ የሆነ ኃይለኛ መልእክት በማስተላለፍ ላይ ይገኛል። ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ፥ ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው” (መዝ.59:4)

ታዲያ ይህ በእንዲህ እንዳለ፡ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ የብዙኃን ዜና ማሰራጫዎች ደግመው ደጋግመው የሕዝቡን ኃይለኛ የልብ ትርታ ለማዳመጥ አሻፈረኝ ይላሉ፥ ክርስቲያኖችንና ክርስትናን፡ ማለትም፡ ኢትዮጵያውያንን በቸልታ ማለፉን ይመርጣሉ። የሬዲዮና የቴሌቪዥን ጣቢያዎች፤ እንዲሁም ጋዜጦችና መጽሔቶች ሁሉ በክርስትና ላይ ለማመጽ በአንድነት ውል የገቡ ይመስላሉ፡ ከእሁድ እስከ እሁድ ያለማቋረጥ የሚያወሩት፡ የሚያሳዩትና የሚጽፉት ስለ ፖለቲካ፥ ስለ ገንዘብ፥ ስለ ዘፈንና ዳንኪራ ብሎም ስለ እንግሊዝ እግርኳስ ጨዋታ ብቻ ነው።

የክርስትና እምነታቸው በተሸረሸረባቸው የምዕራቡ ኢዱስትሪ አገሮች እንኳ ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች በየሰንበቱ የጸሎት ስነሥርዓት ከዓብያተ ክርስቲያናት በቀጥታ ያስተላልፋሉ። የክርስቲያኖች ደሴት በሆነችው ኢትዮጵያ ግን ቴሌቪዥኑ በቅዱስ ሰንበት ፈጣሪን በትንሹም ቢሆን በማስታወስ ፈንታ፡ እንደ ኢትዮጵያን አይደልወይም ፖሊስና እርምጃውየመሳሰሉት ፕሮግራሞች ደጋግሞ ማቅረቡን ይመርጣል። ጸረክርስትና፡ ጸረክርስቲያን እየሆኑ በመጡት የአሜሪካ እና አውሮፓ አገሮች የዜና ማሰራጫዎች እንደ ፋሲካእና ገናለመሳሰሉት በዓላት የሚሰጡት አትኩሮት አሁንም አልቀነሰም፤ ሪዲዮና ቴሌቪዥን ጣቢያዎች በዓላቱ ከመድረሳቸው ከሣምንታት በፊት ነው የገና ዜማዎችን የሚያሰሙት፥ ምርጥ የገና ዜማ ሰሌዳዎችንም ያወጣሉ፤ የሮማው ፓፓስ ሆኑ ነገሥታቱና የአገር መሪዎቹ ሁሉ ለሕዝቦቻቸው የሚያቀርቡትን መልዕክት በሬዲዮና ቴሌቪዥን በቀጥታ ያስተላልፋሉ። ቀንደኛ ኢአማንያን እንደሆኑ የሚታወቁት እንደ Bill Mahr የመሳሰሉት ታዋቂ አሜሪካውያን የቴሌቪዥን ሰዎች ሳይቀሩ አሁንስ በዛ! ከቤተሰብ ጋር አብረን የምናከብረውን የገና በዓላችንንማ አንነጠቅምበማለት እየመጣ ወዳለው አስከፊ ጊዜ ይጠቋቁማሉ።

ታዲያ በpolitical correctness (ይሉኝታ)በሽታ የተለከፈው   የምዕራቡ ዓለም እንኳ ማንነቱን ገና ሙሉ በሙሉ ለመካድ ሳይነሳሳ፡ ለምንድን ነው የኛዎቹ መሪዎች፡ ጋዜጠኞችና ጣቢያዎቻቸው አባቶቻቸው ለታገሉለትና ለሞቱለት የክርስትና ሕይወት ግድየለሽነትን የሚያሳዩት? በትዕግስተኛውና በዝምተኛው ሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታን እያሳደረ የመጣውን ይህን ሁኔታ አይተው አስፈላጊውን የማሻሻያ እርምጃ ለመውሰድስ እስካሁን ለምን ተሳናቸው?

_____________________________________________________

Posted in Ethiopia, Media & Journalism | Tagged: , , , | Leave a Comment »

On The Fall of Man

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 10, 2011


St. John Maximovitch

The world was created good and called to the joy of life in union with the Source and Creator of life, the Lord God.

The first to sin and to be torn from this union were angels. The angelic realm was split: some remained with God; others, in their pride, desired to live their own life, independent of God. The angelic world was split and sin was born there, but the earthly world remained good.

And then the devil, which means “the one cast down from heaven,” began to strive to join the earthly realm to himself. The highest creation on earth, man, had been given a commandment by God not to eat of the tree of knowledge of good and evil. Why was the commandment given? This tree was just like all the others, and in itself it had no outstanding characteristics. No, the knowledge of good and evil was not in the tree itself, and not for this reason was the commandment given. The Lord gave it because man was created free, and the Lord desires of man a freely-willed striving and longing for union with God. The commandment was given because only through its fulfillment could man express his freely-willed striving toward God and love for Him. And blessedness consists simply of communication with God through love of Him.

The devil is burdened by his separation; he is perpetually in a state of wrath and vengeance, and it comforts him to attract others. The devil never appears as his true self, but takes on various appearances. Then in paradise he took on the appearance of a serpent, and gave man the idea that the commandment had not been given for the expression of man’s love of God, but so that man would not become like God. The devil planted the thought that the command was issued, not out of God’s love, so that man would dwell in God’s love, but because God desires to dominate, and to prevent man from being as God, and coming to know the endless and limitless joy of being.

When man came to believe this diabolical idea, he was instantly separated from God. Everything changed, and man could no longer enjoy life in God and speak with God freely and straightforwardly as children speak. There was no peace, no joy, and man began to hide from God. Everything changed, the link between God and man was destroyed and nature ceased to heed man. Weeping entered the world, and the soul became burdened.

______________________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Leave a Comment »

Historical Videos On / From Ethiopia

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 4, 2011


Very interesting to notice that Addis’ stadium goers back then seemed to be stylish, glamorous and elegant – compared to the beer-powerd fanatics of the current footbal world.

The archive has an amazing collection of Cinemagazines and Video-newsreels which is to be found at British Pathe – one of the oldest media companies in the world

________________________________________________________

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , | Leave a Comment »

ታላቋ ብሪታኒያ ስታንስ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 4, 2011


ኢትዮጵያ አገራችን ጠላቶቿ የበዟባት አገር መሆኗ የሚያጠያይቅ አይደለም። ሆኖም አሁን በምንገኝበት ዘመን በተለይ ከአውሮፓ አገሮች በኩል እየተካሄደ ያለው የጥላቻና የተንኮል ዘመቻ በጣም አሰልች እና ኋላ ቀር መስሎ ይታያል። ብዙ ነገሮችን በግልጽ አይተን መረዳት በምንችልበት ዘመን፡ እነዚህ የአውሮፓ ኃይሎች መልካቸውን እየቀያየሩ ሲመጡብን ስናይ፡ ይህ ለኛ ያላቸው ጥላቻ ምን ያህል ሥር የሰደደ ቢሆን ነው ያሰኛል።

በዚህች ምድር ላይ አገራቱንና ሕዝቦችን እንደ እንግሊዞች ሲያበጣበጥ የቆየ ሕዝብ የለም። ከምስራቅ አፍሪቃ እስከ መካከለኛው ምስራቅ፤ ከደቡብ እስያ እስከ ባልካን አገሮች ድረስ የሚታየው ውጥንቅጥ እንግሊዞች ከቀበሩት መርዝ የተነሳ ነው።

አገራችን ተደላድላና ጠንክራ አንድነቷንም አጽንታ እንዳትኖር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ እንግሊዝ አሁንም እየሞከረች ነው። ከ10ሺህ ኪሎሜትር በላይ እየተጓዘች ከአርጀንቲና ጋር ሆነ ከኢራቅና አፍጋኒስታን ጋር ጦርነት የምትገጥመዋ እንግሊዝ ለኦጋዴን ነዋሪዎች ተቆርቋሪ መስላ በኢትዮጵያውያን ጉዳይ ላይ ጣልቃ በመግባት ሁከት ለመፍጠር ትሞክራለች። የኦጋዴን ነፃ አውጭ ድርጅት በሚል መጠሪያ ሥር ለሚታገሉት አክራሪ እስላሞች የሞራልና የገንዘብ እርዳታ ታቀብላለች፡ በለንደን ከተማም ጽህፈት ቤት እንዲከፍቱ ፈቅዳለች። በጣም የሚገርመው፡ 15 ሚሊየን ለሚጠጉ ጭቁን ኩርዶች ከ20 ዓመታት በላይ የሚታገለው የቱርኩ ኩርዳውያን ነፃ አውጭ ድርጅት (PKK) ፡ እንኳን ጽህፈት ቤት ሊኖረው፡ የሽብር ፈጣሪ ድርጅት ነው ተብሎ በምዕራባያውያኑ ዘንድ ለመኮነን በቅቷል። በኢትዮጵያና በእስራኤል ላይ ግን የሌባ ጣታቸውን ቀድመው ይሰዳሉ።

እየተበላሸና ዋጋ ቢስ እየሆነ የመጣው የቀድሞው አንጋፋ የዜና ማሰራጫ ድርጅት፡ ቢቢሲ፡ በኢትዮጵያ እና በእስራኢል ላይ፥ በአፍሪቃ እና በጥቁር ሕዝቦች ላይ፡ በክርስትና እና ክርስቲያናዊ በሆነ ሞራል ላይ ታይቶ ተሰምቶ የማይታወቅ የጥላቻ ፕሮፓጋንዳ በመንዛት ላይ ይገኛል።

ከጥቂት ሣምንታት በፊት በእንግሊዝ ፖሊሶች አንድ ጥቁር እንግሊዛዊ ተገደለ። ይህን ግድያ በመቃወም ብዛት ያላቸው ጥቁሮች አቤቱታቸውን ሰላማዊ በሆነ መልክ በሰልፍ ለመግለጽ ሞከሩ። ይህም ሰላማዊ ሰልፍ ያስደነገጣቸው ባለሥልጣናት ለዓመታት ያዘጋጇቸውን የከተማ ዱርየዎችና ቦዘኔዎች ቀስቅሰው በመጥራት በየከተሞቹ ብጥብጥ እንዲፈጥሩ አደረጉ። የባለሥልጣኑ ዓላማም የማርቲን ሉተር ኪንግ ዓይነት እንቅስቃሴ በእንግሊዝ ጥቁሮች ዘንድ እንዳያድግ ገና በእንጭጩ ለመቅጨት ነው።

ምንም እንኳን ብጥብጥ ፈጥረው የነበሩት ግለሰቦች አብዛኞቹ ነጮች እና እስያውያን ቢሆኑም፡ እንደ ቢቢሲ የመሳሰሉት የዜና ማሰራጫዎች፡ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ ጥቁሮችን ወነጀሉ። ይህን ፕሮግራም ከ ቢቢሲ ዎርልድ ሰርቪስ ያዳምጡ

ቢቢሲን ወይም ሲ ኤን ኤንን ብናይ የዜና አንባቢያንና ቃለ አቀባይ ሆነው የሚያገለግሉት አብዛኞቹ ጋዜጠኞች የፓኪስታን፡ የህንድ ወይም እስላማዊ አመጣጥ ያላቸው ግለሰቦች ናቸው። አንድ ሁለት ጥቁር ጋዜጠኞች በቴሌቪዥን ብቅ ቢሉ፡ ለቴሌቪዥን ፈጽሞ አመቺ ያልሆኑት እየተመረጡ ነው። ችሎታውና ብቃቱ ያላቸው ብሎም ተወዳጅ ሊሆኑ የሚችሉ ብዙ አፍሪቃውያንና ጥቁሮች አሉ፡ የዜና ማሰራጫዎቹ ግን ሊቀጥሯቸው አይፈልጉም፡ ከአጀንዳቸው ጋር አይሄድምና። በጣም የሚገርመውና የሚያሳዝነው፣ የቢቢሲ አብዛኛው ተመልካች ሆነ አድማጭ አፍሪቃ የሚገኝ ነዋሪ መሆኑ ነው። እስያው፡ አረቡ ሆነ አውሮፓዊው የየራሱን ቴሌቪዥንና ራድዮ የሚከታተል በመሆኑ ቢቢሲን የሚከፍተው ጥቂቱ ነው።

በለንደኑ ብጥብጥ ወቅት ጠቅላይ ምኒስትር ዴቪድ ካሜሮን ከጽህፈት ቤታቸው ከዳውንኒን ስትሪት ሆነው ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጡ ከጀርባቸው የሕንጻው ጠባቂ ሆኖ የሚታየው ፖሊስ ጥቁር መሆኑን ለማሳየት ካሜራው በሁለቱ ላይ አተኩሮ ነበር። ጥቁር ፖሊስ ከዚህ በፊት በጽሕፈት ቤቱ ታይቶ አይታወቅም። እዚህ ይመልከቱ።

ቢቢሲ ኢትዮጵያን የሚመለከት ነገር ሲያቀርብ ንቀትና ጥላቻ በተሞላበት መልክ ነው። አንዳንዴ ፖሰቲቭ የሆኑ ወሬዎችን ጣል ስለሚያደርግ ሚዛናዊ የሆነ ነገር የሚያቀርብ መስሎ ሊታየን ይችላል፡ ይህ ግን ረቂቅ ማደንዘዣ፡ ከዜና ማሰራጫው እንዳንርቅ የማድረጊያ ስልቱ እንጅ ሃቅ የጠማው ድርጅት ስለሆነ አይደለም። ይህ ኒዮሊበራል የዜናና ፕሮፓጋንዳ አሰራጭ ድርጅት ጸረኢትዮጵያ፣ ጸረአፍሪቃ፣ ጸረእስራኤል እና ጸረክርስትና የሆነ አጀንዳ እንዳለው አጠንቅቀን ማወቅ ይኖርብናል።

ለምሳሌ፡ በሶማሊያ የተከሰተውን ረሃብ በሚመለከት አስቀድሞ እና ደግሞ ደጋግሞ ረሃብ በምስራቅ አፍሪቃ” “ረሃብ በአፍሪቃው ቀንድእያለ መላው ምስራቅ አፍሪቃን በማጠቃለል እንዲሁም የ 1985 .ምህረቱን የኢትዮጵያ ረሃብ ከልሶ ከላልሶ በማንሳት የኢትዮጵያ ስም ሁሌ ከረሃብና በሽታ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ማሳወቁን ይመርጣል። በብዙህ መቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሶማሊያዎች ጠላቴ ነው የሚሉት፡ በደጉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ላለፈቱ 20 ዓመታት ጥገኝነት አግኝቶ በሰላም እንደሚኖር ቢቢሲና አጋሮቹ አንዴም አትተውት አያውቁም። ነገር ግን 1000 የሚሆኑ ሶርያውያን ስደተኞች በጎረቤታማዋ ቱርክ ጥገኝነት ሲያገኙ፡ እነ ቢቢሲ ቱርኮች ምን ያህል እንግዳ ተቀባዮችና አስተናጋጆች መሆናቸውን ለተመለካቹና አድማጩ ለማሳወቅ ሲቸኩሉ ይታያሉ።

ከጥቂት ሣምንታት በፊት ደግሞ ቢቢሲ ኢትዮጵያውያን የባሪያንግድ ያካሂዱ እንደነበር ለማሳወቅ ደቡብ አፍሪቃ ድረስ ሂደው የአንዲት የቀድሞ ኢትዮጵያዊት የሕይወት ታሪክ አቀረቡልን። በዚህም አማካይነት የኢትዮጵያን አኩሪ ታሪክ፡ ጽኑ ሃይማኖት ባጠቃላይ ኢትዮጵያውያንን ኢትዮጵያውያን ያሰኛቸውን ማንነት ለመተናኮል ይሞክራሉ። እኛ አውሮፓውያን ብቻ ሳንሆን፡ አኩሪ ታሪክ አለን የሚሉት ኢትዮጵያውያንም ኢሰብዓዊ የሆነ ታሪክ ሲፈጽሙ ነበር፡ ኢትዮጵያውያን በባርነት ሲሰማሩ እኛና በአፓርታይድ ሥርዓት የምትታወቀው የነጮቹ ደቡብ አፍሪቃ፡ ኢትዮጵያዊዋን ባሪያ የአስተማሪ ሙያ እንዲኖራት ረድተናት ነበር፡ ለማለት ነው ነገሩ። የተንኮሉን ጥበብ የተካኑት እንግሊዞች የሰላሳ፡ የሃምሳ የመቶ ዓመታት መርዛማ ዕቅድ ነውና የሚያዘጋጁት፡ ፍላጎታቸው አሳዛኝ በሆነ መልክ የተከፋፈሉት የኢትዮጵያ ጎሣዎች እርስ በርሳቸው እየተኮረኳኮሙ እንዲደክሙ እንዲወድቁ፡ ይህን አጋጣሚ ተጠቅመው የመንፈስ እና የጥሬ ዕቃ ጥማታቸውን ለማርካት ይመኛሉ።

19ኛው ክፍለ ዘመን በስዊድን አገር ነግሠው የነበሩት ጉስታቭ 3ኛ የኢትዮጵያ ቡና‘ “መርዝ ሳይሆን አይቀርምብለው ጠረጠሩ። ይህንም ለማረጋገጥ ሁለት የወህኒ ቤት እስረኞች ተመርጠው አንደኛው ቡና ሁለተኛው ደግሞ ሻይ እንዲጠጡ ተደረጉ። ይህንንም ጥናት ለዓመታት እንዲከታተሉ የስዊድን ሊቆች ተመረጡ። እስረኞቹ ቡናቸውንና ሻያቸውን ፉት እያሉ ለብዙ ዓመታት ቆዩ፡ በዚህ ወቅት፡ መጀመሪያ ሊቆቹ ሞቱ፡ ከዚያም ንጉሥ ጉስታቭ፡ በመጨረሻም ሻይ እንዲጠጣ የተደረገው እስረኛ አረፉ። ቡና ጠጪው ግን የወህኒ ቤት ጊዜውን ጨርሶ ወጣ።

ከኢትዮጵያ በፊት ታላቋ ብሪታንያ ቀድማ እንደምትከፋፈል፡ ይህንም በህይወታችን ለማየት እንደምንበቃ እርግጠኛ ነኝ። ይህ ታታሪ የብሪታኒያ ሕዝብ በዚህ መልክ አሁን እየወደቀ መምጣቱ ሊያስገርመን አይገባም።

 

_________________________________________________________

 

 

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: