Archive for December, 2010
George Clooney Eyes Sudan
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 31, 2010
Posted in Ethiopia | Tagged: George Clooney, Referendum, Sudan | Leave a Comment »
ትክክለኛው የዘመን አቆጣጠር
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 31, 2010
- “ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት“ ከሚለው የንቡረ እድ ኤርምያስ ከበደ ወልደ ኢየሱስ መጽሐፍ የተወሰደ…
በአረማዊነት ባህል፡ በክዋክብት ሥነ እውቀት ላይ የተመሠረተው የምዕራባውያን የዘመን አቆጣጠር፡ ከኢትዮጵያውያኑ የዘመን አቆጣጠር፡ የሚለይበት ባሕርይና አኹን ያለበት ቀውስ የደረሰበት ለምን ይሆን?
ኢትዮጵያውያን፡ በቅዱሱ ኪዳን ሃይማኖታቸው ላይ የመሠረቱትን፡ ይህን የጊዜ አቆጣጠር ሥርዓት፡ ምዕራባውያን፡ ኦርቶዶክሳውያን የተባሉት አብያተ ክርስቲያናት ጭምር፡ በአረማዊው፡ ዮልየስ ቄሣርና ጎርጎርዮስ (ግሬጎሪ) ፩፫ኛ በተባለው፡ በካቶሊካዊው ጳጳስ ስሞች እየሠየሙ፥ በየጊዜው እየለዋወጡና በመጨረሻ፡ ፰ ዓመታት ከ፲ ቀናት ያህል አክለውበት መቆየታቸው ይታወቃል። በዚህ የአቆጣጠራቸው ስልት፡ የጌታችን የኢያሱስ ክርስቶስን የልደት ቀን፡ ከ፬ እስከ፯ ዓመታት ለሚደርስ ዘመን፡ ከፍ አድርገው እንዲጨምሩ በመገደዳቸው፡ ይህን፡ ሰው ሠራሽ ቀውስ አስተካክለው ለማስታረቅ አቅቷቸው፡ እነሆ፡ እስካሁን ሲባዝኑ ይገኛሉ። በዚህ፡ በእነርሱው አቆጣጠር፥ ጌታ፡ የተወለደው፡ “በ፬፥ በ፮ ዓመተ ምሕረት ላይ ሳይኾን አይቀርም” ከማለት በስተቀር፡ እርግጠኛውን ቀን፡ በቁርጥ ሊወስኑ ሳይቻላቸው ቀርቷል።
ይህ ቀውስ የተፈጠረባቸው፡ የጌታን የልደት ዓመት፡ አንድ ብለው መቁጠር ከጀመሩ በኋላ፡ ያ፡ የዓመተ ምሕረት መነሻ ዘመን፡ በአረማዊነት ዘመናቸው፡ “ጁልያን” በሚል ስምና በተለያየ ስልት ይጠቀሙበት በነበረው የአቆጣጠር ሥርዓታቸው፡ በ፬፥ በ፯ ዓመታት ላይ ውሎ ስላገኙት ነው።
ሌላው፡ ይህን ችግር የፈጠረባቸው ምክንያት፡ የምዕራባውያን የጊዜ አቈጣጠር፡ እንደ ኢትዮጵያውያኑ፡ በአንድ መሠረት ላይ ታንጾና በአንድ በተስተካከለ ሥርዓት ተቀምሮ የሚመራ ባለመኾኑ ነው። ይህንም፡ ከዚህ የሚከተለውን ማነጻጸሪያ ሓተታ በመመልከት መረዳት ይቻላል።
ኢትዮጵያውያን፡ “የእግዚአብሔር ገነት” ተተከለባት፡ አዳምና ሔዋን የተፈጠሩባት አገራቸው የምትገኘው፡ በምድር ማዕከል ወይም መቀነት ክልል ውስጥ ስለኾነ፡ የጊዜ አቈጣጠራቸው ሥርዓት፡ መዓልቷና ሌሊቷ፡ ዓመቱን ሙሉ፡ በ፲፪፡ በ፲፪ ሰዓታት፡ እኩል በተከፈለበት የአሠፋፈር ስልት ላይ ተመሥርቶ፡ የባሕረ ሓሳቡ ቅመራ፡ ሥርዓቱን ጠብቆ፡ ያለችግር ይካኼዳል። ይኽውም፡ ወደኋላ፡ ወደረቂቃኑ ሳንኼድ፡ ከሣልሲት ተነሥተን፡ እስከ ዓመት ብንቈጥር እንኳ፡ ቀመሩ፡ የተስተካከለ ኾኖ እናገኘዋለን። ማለትም፡ ፷ (ስድሳ) ሣልሲታት፡ ፩ (አንድ) ካልዕት (second)፥ ፷ ካልዕታት፡ ፩ ደቂቃ፥ ፷ ደቂቃት፡ ፩ ሰዓት፡ ፳፬ ሰዓታት፡ ወይም ፷ ኬክሮስ፡ ፩ ዕለት፡ ፩፪ ሰዓታትን የያዘው፡ የብርሃን ጊዜ፡ “መዓልት“፥ ጨረቃ እንድትሠለጥንበት የተፈጠረችበት፡ ፩፪ ሰዓታትን የያዘው፡ የጨለማ ጊዜ፡ “ሌሊት” ይባላል።
የመዓልቱ የጊዜ አቆጣጠር፡ የተፈጥሮውን ሥርዓት በመከተል፡ “ከቀትር በፊት” እና “ከቀትር በኋላ” ተብሎ፡ ፀሓይ፡ ጮራዋን በምትፈነጥቅበት፡ በንጋቱ ፩ ሰዓት ይጀምርና፡ በምትጠልቅበት፡ በምሽቱ ፲፪ ሰዓት ያበቃል፡ የሌሊቱም ጊዜ፡ እንደዚሁ፡ እስከእኩለ ሌሊት ድረስ፡ “ከማታው“፥ ከእኩለ ሌሊት በኋላ ደግሞ፡ “ከሌሊቱ” እየተባለ፡ ጨረቃ ከምትታይበት፡ ወይም ጨለማው ከሚጀምርበት፡ ከምሽቱ፡ ፩ ሰዓት ይነሣና፡ ጎህ በሚቀድድበት፡ በንጋቱ ፲፪ ሰዓት ይቆማል።
በዚህ መሠረት የተደለደለችው፡ አንዲቱ ዕለት፡ ሰባት ስትኾን፡ ፯ቱ ዕለታት፡ ፩ ሳምንት ይኾናሉ።
የምዕራብውያኑ ግን፡ እንዲህ አይደለም። ምዕራባውያን፡ የሰሜኑንና የደቡብን የመሬት ዋልታ ተከትለው፡ በሰሜንና በደቡብ ክፍላተ ዓለማት፡ የሚኖሩ በመኾናቸው፡ ኢትዮጵያውያን፡ ክረምት፥ መፀው፥ በጋ፥ ጸደይ እንደሚሉት፡ የእነርሱም ዓመት፡ Winter(ዊንተር) Spring (ስፕሪንግ) Summer (ሰመር) Autumn (ኦተምን) በተባሉ፡ በአራት የተለያዩ ወራት ተከፋፍሎ፡ በክረምቱ፡ ሌሊታቸው፡ እስከ ፭ ሰዓታት የሚጨምርበት፥ እንዲያውም፡ ወደሰሜኑም ኾነ ወደ ደቡቡ የመሬት ዋልታ ጫፍ እይተጠጉ በኼዱ መጠን፡ የሚቀነሱት፡ ወይም የሚጨመሩት ሰዓታት እያደጉ ይኼዱና፡ ወደ መጨረሻው ጽንፍ ላይ ሲደርስ፡ ከናካቴው፡ ፮ ወራት ሙሉ፡ ሌሊት ብቻ፥ ወይም መዓልት ብቻ ይኾናል።
ይህም ማለት፡ ይህ ኹኔታ፡ በሰሜኑና በደቡቡ ክፍላተ ዓለም፡ በዓመቱ ውስጥ፡ እንዲህ ስለሚፈራረቅ፡ የክረምቱ ብርዳማ ጠባይ፡ ቀደም ብሎ እንደተገለጸው፡ የሰሜኑን ክፍል በሚያጠቃበት ጊዜ፡ በደቡቡ ክፍል ደግሞ፡ የበጋው ፀሓያማ ጠባይ ይሰፍናል ማለት ነው።
ይህ ብቻ ሳይኾን፡ በዓመት፡ ሁለት ጊዜያት፡ በየ፮ ወሩ፡ የሰዓት አቆጣጠራቸውን፡ እንደየክፍለ ዓለማቸው አቀማመጥ፡ በ፩ ሰዓት ያሳድጉታል፡ ወይም በ፩ ሰዓት ይቀንሱታል።
በኢትዮጵያውያን ዘንድ፡ ፯ቱ የሳምንቱ ቀኖች፡ የእግዚአብሔር፡ የሥነ ፍጥረት ሥራው፡ በተራና በቅደም ተከተል የተካሄደባቸውንና በቅዱሳት መጻሕፍት የተመዘገቡትን የዕለታት ስም እንደያዙ፡ የአዳምና ሔዋን ቋንቋ በሆነው፡ በግእዝ፡ “አሐዱ“፡ “አንድ“፡ ወይም፡ “መጀመሪያ ቀን” ለማለት፡ “እሑድ“፥ ቀጥሎ፡ “ሁለት“፥ ወይም፡ “ሁለተኛ ቀን” ለማለት፡ “ማግሰኞ“፡ ቀጥሎ፡ “አራት“፥ ወይም፡ “የሰንበት መግቢያ” ፥ ወይም፡ “የሳምንቱ ጊዜ፡ የሚጠልቅበት ቀን” ለማለት፡ “ስድስተኛው ቀን“፡ “ዓርብ“፥ በሰንበት ጌታ፡ በኢያሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ፡ “ወደዘለዓለማዊነት” ከመለወጧ በፊት፡ ቀድሞ የነበረችበትን ሁኔታ ለማስታወስ፡ “ሰባተኛዪቱን የሰንበት ቀን“፡ “ቅዳሜ” ብለው ይጠርዋቸዋል።
ምዕራባውያን ግን፡ ለእነዚሁ የሳምንት ቀኖች፡ የሰጧቸውን የአረማውያን ጣዖታት አማልክቶቻቸውን ስም እንመልከት!
-
Sunday: Sun’s day (ሳንዴይ) ማለት የፀሓይ ቀን፥
-
Monday: Moon’s day (ማንዴይ) የጨረቃ ቀን፥
-
Tuesday: Tui’s day (ቱዩስዴይ)፡ ማለት፡ የጦርነቱ አምላክ፡ የቲዩ ቀን፥
-
Wednesday: Woden’s day (ዌድንስዴይ)፡ ማለት፡ የታላቁ አምላክ የውድን ቀን፥
-
Thursday: Thor’s day (ተርስዴይ)፡ ማለት፡ የነጎድጓዱ አምላክ፡ የቶር ቀን፥
-
Friday: Frigg’s day (ፍራይዴይ)፡ ማለት የታላቁ አምላክ፡ የዎድን ሚስት፡ የፍሪግስ ቀን፥
-
Saturday: Saturn’s day (ሳተርዴይ)፡ ማለት፡ የሰማዩ ኮከብ፡ የሳተርን ቀን።
በኢትዮጵያውያን ዘንድ፡ ፴ ዕለታት፡ ፩ ወር ሲኾኑ፥ ፲፪ ወራት እና ፭ ዕለታት ተሩብ ደግሞ፡ ፩ ዓመት ይኾናሉ። ፭ቱ ዕለታት ተሩብ፡ “ጳጉሜ” ይባላሉ። “ጳጉሜ“፡ የቃል ለቃል ትርጉሙ፡ “ተውሳክ“፡ “ጭማሪ“፥ “ተረፍ“፡ “ትርፍ” ማለት ነው። ፲፪ቱ የምዕራባውያን ወሮች ግን፡ ፳፰፡ ዕለታትን፥ በየአራት ዓመቱም፡ ፳፱ ዕለታትን ከያዘውና (February – ፌብሩአሪ) ከሚባለው፡ ከአንደኛው ወር በቀር፡ እኩሌቶቹ፡ በ፴፥ የቀሩትም፡ በ፴፩ ዕለታት ተመድበው፡ ይህን በመሰለ የተዘበራረቀ መልክ ይቆጠራሉ።
በኢትዮጵያውያን በኩል፡ ከመስከረም እስከ ነሓሴ ድረስ ያሉት፡ ፲፪ቱ ወሮቻቸውና ጳጉሜ፡ እያንዳንዳቸው የሚጠሩበት ስም፡ ከእግዚአብሔር ከተሰጣቸው፡ የተፈጥሮ ጸጋቸው ጋር የተያያዘው ገጽታቸውን የሚያሳይ ትርጉም ያለው ሲኾን፡ በኢትዮጵያውያን የወራት አመዳደብ መሠረት፡ ከ September (ሴፕቴምበር) መስከረም እስከ እስከ August (ኦገሥት) ነሓሴ ድረስ ያሉት የምዕራባውያኑ ወሮቻቸው ግን እንደሳምንቱ ቀኖቻቸው ኹሉ፡ የተሠየሙት፡ በጣዖቶቻቸውና እንደአማልክት ይሰግዱላቸው በነበሩት ገዢዎቻቸው ስም ኾኖ ይገኛል።
ይኽውም፡ መስከረምን ከኢትዮጵያውያን፡ Augustን (ኦገሥትን) ነሓሴን ደግሞ ከምዕራባውያን፡ ለምሳሌ ያህል ወስደን ብንመለከታቸው “መስከረም“፡ በኢትዮጵያኛ፡ “ከረመ” ወይም፡ “ክረምትን አሳለፈ” ከሚለው ግሥ ወጥቶ፡ “ክረምቱ የሚያበቃበት፡ ማለትም፡ የዝናሙ ጠል አብቅቶ፡ የፀሓይ ብርሃን የሚፈነጥቅበት፡ የዓባይና የሌሎቹ ወንዞች ሙላት መጉደል የሚጀምርበትና ፍጥረቱ ኹሉ፡ ከተሸሸገበት በዓቱ እየወጣ፡ እርስ በርሱ የሚገናኝበት፡ አዲሱ ዓመት፡ የሚገባበት ማለት ነው። “መስከረም ጠባ” የሚባለውም ለዚህ ነው። በምዕራባውያን ዘንድ ግን፡ August (ኦገሥት)፡ ስለወሩ ኹኔታ፡ ምንም ትርጉም የሌለው ኾኖ፡ እንደጣዖት ይመለክ ለነበረው፡ ለአረማዊው ርእሰ ነገሥት (Emperor): ለአውግሥጦስ ቄሣር፡ በመታሰቢያነት የተሰጠ ወር መኾኑን ብቻ ያስረዳል።
የኢትዮጵያውያን ዓመት የሚጀምረው፡ በ“መስከረም“፡ የሚያበቃውም፡ በ“ጳጉሜ” ሲኾን፡ የምዕራባውያ ኑ ግን፡ በእነርሱ January (ጃንዋሪ)፡ ማለትም፡ በ“ጥር” ይጀምርና፡ በDecember (ዲሴምበር)፡ ማለትም በ“ታኀሣሥ” ይጨርሳል። ስሙን በመታሰቢያነት፡ January (ጃንዋሪ) ብለው፡ ለዓመቱ የመጀመሪያ ወር የሰጡለት፡ Janus(ጃኑስ)፡ ለሮማውያን፡ ታላቁ ጣዖታቸው እንደነበረ፡ ቀደም ብሎ ተመልክቷል።
በኢትዮጵያውያን ዘንድ፡ ፬ ዓመታት፡ ፩ ዐውደ ዘመን ይኾናሉ። ይህም፡ እያንዳንዱ ዓመት፡ ፫፻፷፭ ከሩብ ዕለታት፡ ወይም ከ፮ ሰዓታት፡ ወይም ከ፲፭ ኬክሮስ ያለው ሆኖ፡ “ዘመነ ማቴዎስ“፥ “ዘመነ ማርቆስ“፥ “ዘመነ ሉቃስ” እና “ዘመነ ዮሓንስ” ተብሎ ተሠይሟል፡ እነዚህ፡ የ፬ቱ ዓመታት ጳጉሜዎች ሰዓታት ሲደመሩ፡ ፩ ዕለት የሞሉና፡ በ፬ኛው ዓመት፡ በዘመነ ዮሓንስ መግቢያ፡ ፮ ዕለታት በመሆን፡ የባሕረ ሃሳቡ ቅመራ ይካተታል፡ የዘመን አቆጣጠሩም ዐውድ፡ እንዲህ በየአራት ዓመታቱ ይዘጋል።
ስለዚህ፡ “የግሬጎሪ” ወይም “ግሬጎሪያን” ተብሎ የሚጠራው፡ የምዕራባውያን፡ የጊዜ አቆጣጠር ባህል፡ እንዲህ፡ ምስቅልቅሉ የወጣ በመሆኑ፡ በእርሱ ሰበብና ጠንቅ፡ ጽኑ የሆነው ሃይማኖታዊና ተፈጥሮአዊ መሠረት ያለው፡ የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ሥርዓት፡ ሊቃወስ ቀርቶ፡ ሊነካ እንኳ፡ ከቶ አይገባም።
Posted in Ethiopia | Tagged: Calendar, Calendar Systems, Enochian Calendar, Ethiopian Calendar, Gregorian Calendar, Julian Calendar | Leave a Comment »
Researcher Identifies Second-Oldest Ethiopian Manuscript in Existence in HMML’s Archives
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 18, 2010
Ted Erho, a doctoral student at Durham University in England, recently spent six weeks at HMML studying Ge’ez (classical Ethiopic) manuscripts, according to Hill Museum & Manuscript Library.Com.
HMML’s microfilm and digital collections are the richest resource for the study of Ethiopian manuscripts in the world. Supported by one of HMML’s Heckman scholarships, Erho made stunning discoveries for both Ethiopian and biblical studies during his time at HMML.
Working with previously-uncataloged manuscripts from HMML’s Ethiopian Manuscript Microfilm Library, Erho has identified the second oldest Ethiopic manuscript in existence (the oldest is the famous Abba Garima Gospels), which also contains the oldest known copies of books from the Old Testament.
This manuscript, EMML 6977, dates prior to the Solomonic Era in Ethiopia, which began in 1270 CE and contains the books of Job and Daniel, as well as two homilies. He also identified the oldest known major Ge’ez codex of the Old Testament (EMML 9001), which contains the entire Book of Jubilees, considered to be a canonical book by the Ethiopian Orthodox Church. Its presence in this manuscript is now the oldest known copy of the Book of Jubilees.
Finally, Erho is cataloging the biblical manuscripts from Gunda Gunde in northern Ethiopia, numbering more than fifty of the 220 manuscripts in the Gunda Gunde collection photographed in 2006 by Michael Gervers and Ewa Balicka-Witakowska in an expedition sponsored by HMML.
All but one of the Old Testament manuscripts at Gunda Gunde are from the sixteenth century or before, exceptionally early for Ethiopian manuscripts.
Posted in Ethiopia | Tagged: Ethiopia, Ethiopian Manuscript, Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, Gunda Gunde Collection | Leave a Comment »
Ethiopian Monasteries – Relevant or Relic?
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 1, 2010
The Ethiopian Orthodox Church is struggling to maintain its monastic traditions in the wake of the Marxist nationalization of monastic properties in the late twentieth century.
“Under Marxist Derg rule, which lasted until 1991, the government seized and redistributed church-owned land,” ONE Magazine reports. “Monasteries, which traditionally operated relatively large farms, were forced to forfeit much of their property and, as a result, lost their economic sustainability. Stripped of their resources, monks and nuns also surrendered their vital roles as producers, employers, educators and leaders in their communities.”
0.8% of Ethiopia’s 77.2 million people are Catholic, according to Vatican statistics; 51% are Ethiopian Orthodox, 33% are Muslim, and 10% are Protestant. The Ethiopian Orthodox Church ceased to be in communion with the Holy See following the Council of Chalcedon in 451.
Sunrise at the Meskaye Hizunan Medhane Alem Monastery in Addis Ababa, Ethiopia’s capital and largest city, feels anything but contemplative. A cacophony of roaring bus and car engines interrupts the early morning calm. A blur of red brake lights eclipses the rising sun’s soft rays. The compound, which includes a church and an elementary and high school, sits at the heart of the bustling Sidist Kilo neighborhood, home to Addis Ababa University’s main campus. The neighborhood’s urban energy is palpable, even when the city has barely awakened.
Inside the church, worshipers and monks have filled the pews to celebrate the day’s first liturgy. Chants drown out the noise of the street. Incense meanders through the candlelit nave.
As the service concludes, Abbot Melake Girmai leads the monks to the monastery’s refectory. A small army of kitchen staff serves a hearty breakfast — fluffy white injera (spongy bread made from teff), wat (a traditional vegetable and meat stew), fruit, coffee and tea.
Though hardly the lap of luxury, the monks at this urban religious house enjoy comforts unthinkable in the far more ascetic rural monasteries for which Ethiopian Orthodoxy has long been known.
No one bears witness better to this contrast than Abba Kidane Mariam Arega, who has just arrived in the capital from the rural Georgis of Gasicha Monastery in Wollo. He is on his way to visit old friends at the Ziquala Monastery, a day’s journey from Addis Ababa.
Before dawn the next day, Abba Kidane sets out for Mount Ziquala, an extinct volcano whose peak is home to the monastery. For the next two hours, he drives along the dusty highway that cuts through the golden plains of Ethiopia’s Rift Valley.
Little by little, the sun’s morning rays illuminate the landscape. Nearing Mount Ziquala, the two-mile-high peak casts a wide shadow on the valley. As the sun climbs above the mount, its shadow gradually draws back as though a stage curtain, revealing an ageless vignette — peasants with donkeys tending their fields.
Arriving at the base of the mountain, Abba Kidane pulls into Wanbere Mariam, a small farming village whose outward appearances have not changed in centuries. Only pop music pulsating from an unidentifiable source situates it in the new millennium.
The drive may be over, but the journey is certainly not. The summit of the mountain may only be reached by hiking three hours on a winding trail. Despite the steep, rocky terrain, the monk displays no physical strain, even as his flowing black cassock absorbs the sun’s now blistering rays. The trail’s switchbacks steepen as they climb the mountain; the thick shrubs give way to forest.
Finally, the trail levels out and opens onto a swath of terraced fields. Sweeping panoramic views of the countryside are visible in almost every direction. A weathered sign welcomes visitors to the Ziquala Monastery, where some 230 monks and 120 nuns make their home.
As do Ethiopia’s better known monasteries — Debra Damo in Tigray, Debra Libanos in Shoa and Debra Hayk in Wello — Ziquala exemplifies Ethiopia’s ancient monastic tradition. Its remoteness and the communal and strictly ascetic lifestyle of its residents recall Ethiopia’s first monasteries, which appeared in the fifth century.
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: Ethiopia, Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, Monasteries, Monks, Spiritual Life | Leave a Comment »