Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • December 2009
    M T W T F S S
     123456
    78910111213
    14151617181920
    21222324252627
    28293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Ethiopia Conspiracy

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 14, 2009

ኢትዮጵያ ተከባለች

አውሬው ተለቅቋል፡ አውሬው ከግራ ከቅኝ፡ ከላይ ከታች፡ ከውጭ ከውስጥ እያለ ይፈታተነናል። አውሬው በተከታዮቹ አማካይነት ምድረ ሞርያን እና ምድረ ኢትዮጵያን ለመዉረር ዳር ዳር ይላል። የኢትዮጵያ አምላክ ግን እንደተለመደው በኢትዮጵያ ተራሮች ላይ በሠፈረው መንፈሳዊ ሠራዊቱ አማካይነት በዝምታ ይከታተላቸዋል።

ከየመን እስከ ሶማሊያ ከባህረ ገሊላ እስከ ቪክቶሪያ ሃይቅ ድረስ የአውሬው ሠራዊት እየቀበረ ያለውን ወጥመድ የኢትዮጵያ አምላክ ፎቶ በማንሳት ላይ ይገኛል።

የአውሬው አገልጋዮች፡ ሸህ ቢን ላድንን ወደ ሶማሊያ ሃጂ አልሳርካዊንን ደግሞ ወደ ጋዛ ለማሸጋገር ዝግጁ ይመስላሉ፡ እስካሁን ካልተሸጋገሩ።

ሊያውቁትና ሊቀበሉት ያልፈለጉት የእስራኤል አምላክ ቅዱስ መንፈስ በምድረ ኢትዮጵያ እንደሚገኝ ደርሰውበታል። ኢትዮጵያን ሊደፍሩ ይፈልጋሉ፡ ግን እስካሁን አልተቻላቸውም፡ ስለዚህ፡ በአውሬው ዓይን ከኢትዮጵያ ጋር በብዙ ነገሮች ተመሳሳይነትን በምታሳየው፡ ነገር ግን የቅዱሱ መንፈስ ተቃራኒ መንፈስ በተንሰራፋባትና የኢትዮጵያ ጆግራፊያዊ የመስተዋት ግልባጭ በሆነችው በአፍጋኒስታን አስፈላጊ ያልሆነ ትኩረት በማድረግ ከፍተኛ መስዋእትን በመክፈል ላይ ይገኛሉ።

በአሜሪካ ግዛቶች ብዙ ጥፋት የሚያስከትሉት አውሎ ንፋሶች መነሻ የኢትዮጵያ ተራሮች መሆናቸውን መመልከት የቻለው የጠፈር መርማሪው አሜሪካዊ ድርጅት፡ “NASA” ለኢትዮጵያ መንግስት በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንደሚከፍል ይታወቃል። የሚገርመውና ብዙዎቻችንን ምናልባት ሊይስደነግጥ የሚችለው ነገር፡ በመስከረም ፩፩ ፪ ሺ ፩ ዓ.. ሽብርተኞች በኒውዮርክ ከተማ ላይ ጥቃት ባደረጉበት በአዲሱ አመታችን መግቢያ እለት፡ “ISS” በመባል የሚታወቀው ዓለም አቀፋዊው የህዋ መመርመሪያ ጣቢያ፡ የኦርቢታዊ ቦታ አቅጣጫው፡ (Orbital Position) ልክ አፍሪቃ ቀንድ ላይ ማረፍ እንደነበረበት፡ ነገር ግን ፕላኑ በጊዜው በስራ ላይ እንዳልዋለ ጭምጭምታዎች መሰማታቸው ነው። ምስጢሩ ምን ይሆን?

ከክትባት እንቆጠብ

..አ በ August 1, 1989.. “The Sun” ተብሎ የሚታወቀው ታዋቂ የእንግሊዝ አገር የመንገድ ወሬ አሳዳጅ ጋዜጣ፡ “Big Brother’s Coming!” በሚል ርዕስ፡ በላብራቶሪ ውስጥ የተፈጠረ የአሳማ ጉንፋን ኤፒደሚ ገብቷል ይባልና የክትባት ዘመቻ ይካሄዳል ፣ ክትባቱ የሚያስፈልግበትም ምክኒያት በዚህ ሰበብ ህዝቡን ሁሉ በጸረክርስቶሱ የአውሬው መርዝ ለመንደፍ በማሰብ ነው የሚል ዘገባ አቅርቦ ነበር።

ጋዜጣው ገና ከ 20 ዓመታት በፊት እንዲህ የሚል ነገር በገጾቹ ላይ አስፍሮ ነበር፡

Coded microchips implanted in every person in the country would tie all of us into a master computer that could track anyone down at any moment, and plans for such a system are already under way whether you like it or not!”

ይቀጥልና

The tiny transmitters can be injected painlessly from a tiny gun in humans without them even knowing it through a nationwide vaccination program.”

በመጨረሻም፡

All the government would have to do is make up something like the swine flu vaccine.”

በማለት ጽፎ ነበር።

እነዚህ የዲያብሎስ አገልጋዮች፡ እንዲህ የመሳሰሉትን ሴራዎች ገና ጥንት ነው ሲጠነስሱ የቆዩት። እግዚአብሔር ይይላቸው፡ እግዚአብሔር ከተንኮላቸው ሁሉ ይጠብቀን።

ባካችሁ እኛ አንተነኳኮል፡ አንድከም፡ በመጨቃጨቅ በመሰዳደብ አውሬውን አንመግብ። እንቀራረብ፡ እንሰባሰብ፡ እንተሳሰብ፡ እንተባበር፡ እንፈቃቀር፡። በኋላ አቅሙም ጊዜውም ስለማይኖረን እንዳይዘገይብን።

http://www.mediafire.com/?mnhltmmyzqn

______________________________________


2 Responses to “Ethiopia Conspiracy”

  1. […] በቀጥታ ምንም ዓይነት የዓካል ግኑኝነት አይኖራቸውም። ከኛ ጋር ግኑኝነት ያላቸው ወይም እኛን የሚቀርቡን ለኛ በጎ የማይመኙልን ወይም እኛን […]

  2. […] ከእነዚህ ሁለት ተቋማት የተገኘው ገንዘብ፡ አትጠራጠሩ፡ ከፈረንሳይ ለመሸመት በታቀዱት ጦር መሳሪያዎች ላይ ይውላል። (የኢትዮጵያን አየር መንገድ፣ ባንክና ቴሌኮምን ለመሸጥ ሲሯሯጥ የነበረውን ሸማቹን ለማ ገገማን ያለምክኒያት የመከላከያ ሚንስትር አላደረገውም። እኅተማርያም አውስታው ነበር) በእነዚህ መሳሪያዎች ላይ ቆላማዎቹ የዋቄዮ–አላህ ልጆች በቂ ስልጠና እስኪያደርጉ ድረስ “አማራ” የሚሏቸውን ተዋሕዶ ኢትዮጵያውያንን እንደ ሐረር ከመሳሰሉት ቆላማ የደቡብ ኢትዮጵያ ቦታዎች ጠራርጎ በማስወጣት ወደ ደጋማዎቹ የሰሜን ክፍለ ሃገራት እንዲሰደዱ ያደርጋሉ። እዚያም “አማራ” የተባለ አዲስ ሃገር እንዲመሰርቱ ይገፋፏቸዋል። አሁን አዲስ ሃገር መስርተናል ካሉ በኋላ “የኛ ነው” የሞሏቸውን እንደ ራያ የመሳሰሉትን ቦታዎች ያስመልሱ ዘንድ ከገዙትና በሱዳን በኩል ከቱርክ የሚገኙትን የጦር መሳሪያዎችን በከፊል ለ”አማራዎች” ያቀብላሉ። በዚህም የተደፋፈሩት ደጋማዎቹ ተዋሕዶ አማራዎች ከደጋማዎቹ ተዋሕዶ ትግሬዎች ጋር ጦርነት ይከፍታሉ፤ ጦርነቱ በሁለቱ ወንድማማች ኢትዮጵያን ላይ እጅግ በጣም የከፋ ዕልቂትና ውድቀትን ያስከትልባቸዋል። በጦርነቱ የደከሙት ተዋሕዶ አምሓርዎችና ትግሬዎች አገግመውና ከሠሩት ስህተት ተምረው እንደገና እንዳይንሰራሩ የአውሬው አብዮት ሠራዊት ከፈረንሳይ የሚያገኛቸውን የኑክሌር ወይም ኬሚካል ተሸካሚ ሮኬቶች ያወርድባቸዋል። በዚህ ወቅት ግብጽና የአረብ ሊግ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ሰተት ብለው ይገቡና በቅኝ ተገዝታ የማታውቀውን ታሪካዊቷን ኢትዮጵያ ይቆጣጠራሉ። የአይ. ኤፍ. ኤምን እና የዓለም ባንክን ብድር መክፈል ያለባት ኢትዮጵያ በጊዜው ስለማትኖር እነዚህ ሁለት የአውሬው ተቋማት የሕዳሴው ግድብ የሚገኝበትን “ቤኒ ሻንጉል” የተባለ ክልል ይወርሳሉ። ክልሉ የተመሠረተው ለዚህ ዓላማና ለዚህ ወቅት ነበር። ኢትዮጵያ ተክብባለች፤ ከሶሪያና ኢራቅ ቀጥሎ ወደ ኢትዮጵያ ይዘምታሉ፡ በተራራማዋ አፍጋኒስታን ለኢትዮጵያ እየተለማመዱ ነው፤ ለማለት ተገድጄ ነበር፡ ከአሥር ዓመታት በፊት፤ ልክ በዚህ ሳምንት፤ ገና የሶሪያው ጦርነት ሳይጀምርና ጥንታውያን ክርስቲያን ወገኖቻችን ለመጨፍጨፍ ሲዘጋጁ። Ethiopia Conspiracy […]

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: